በጎንደር ከተማ አንድ የሚሊሺያ አዛዥ ተገደለ በርካታ ሰዎችም ታሰሩ

መጋቢት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የጎንደር ከተማ የሚሊያሻዎች ሃላፊ ኮማንደር መጋቢት 11 ቀን 2015 ዓም ቀበሌ 15 ወይም ፋሲለደስ ትምህርት ቤት አካባቢ ከምሽቱ 2 ሰአት አካባቢ ላይ ማንነታቸው

ባልታወቁ ታጣቂዎች ተገድሏል። ገዳዮቹም መሳሪያውን ማርከው ከእነ ትጥቃቸው ወደ አርማጭሆ ጫካ መግባታቸው ታውቋል። የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊው ግንባሩ አካባቢ በጥይት የተመታ ሲሆን ወዲያውኑ ህይወቱ አልፏል።

ድርጊቱን ተከትሎ የጸጥታ ሃይሎች አከታትለው በመተኮሳቸው ህዝቡ ሁኔታውን ለማየት  ወደ አደባባይ ሲወጣ  ወደያውኑ መብራት እንዲጠፋ ተድርጓል።

አዣዡ በህዝቡ ላይ የተለያዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ይፈጽም እንደነበር የከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል። የፌደራል ፖሊስ አባላት አሁንም በአካባቢው እያንዣበቡ መሆኑን የአይን ምስክሮች ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ ሰሞኑን ታጣቂዎች ገብተዋል በሚል መንግስት ከፍተኛ ቁጥር ሰራዊት በአብርሃ ጅራ፣ አብድራፊና አጎራባች ከተሞች አሰማርቶ ፍተሻ እያካሄደ ሲሆን፣ የአካባቢው ባለስልጣናትም ሳይቀር ተቃዋሚዎችን ትደግፋላችሁ ተብለው ተይዘዋል።

በመተማ አካባቢ በቅርቡ ለመከላከያ ሰራዊት ደሞዝ ሊከፍሉ በመንገድ ላይ የነበሩ አንድ ኮሎኔል፣ አንድ መቶ አለቃ፣ አንድ ተራ ወታደርና ሹፎራቸው ተገድለው ገንዘቡ በታጣቂዎች ከተወሰደ በሁዋላ ፣ ድርጊቱን የፈጸሙት ወደ አብርሃ ጅራ የገቡ የአርበኞች

ግንቦት7 አባላት ናቸው በሚል ፍተሻ ሲካሄድ ሰንብቷል። ምንጮች እንደሚሉት ታጣቂዎቹ 3 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች፣3 ሽጉጦችንና 250 ሺ ብር የያዘ የገንዘብ መያዢያ ቀረጢት ይዘው ተሰውረዋል።

ታጣቂዎቹ ምእራብ አርማጭሆ ገብተው ምሳ መብላታቸውን፣ የአካባቢውን ነዋሪዎች በሬ ግዝተው መጋበዛቸውንና ስለ አለማቸው ማስረዳታቸውን የሚገልጹት የአይን እማኞች፣ የአካባቢው ነዋሪም ድጋፉን እንደሰጣቸው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በአብድራፊና አብርሃጅራ ከተማዎች  መምህራን፣ አንድ ሴቶች ጉዳይ ውስጥ በሃላፊነት የሚሰራ የመንግስት ሰራተኛ፣ የአካባቢው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ ሃላፊ  ፣ የመንግስት ታጣቂ ሚሊሺያ ተይዘው ታስረዋል። በአካባቢው የታሰሩት ሰዎች ቁጥር ከ20

በላይ መሆኑን ነዋሪዎች ይናገራሉ።

ወደኤርትራበርሃየሚሻገሩኢትዮጵያውንቁጥርመበራከቱንተከትሎ፣በሱዳንጠረፍዙሪያመከላከያሰራዊትየመውጫበር የተባሉትን ቦታዎች ሁሉ ዘግቶ  ጥበቃውን አጠናክሯል።

የአካባቢው ሰዎች እንደሚናገሩት ከተቃዋሚዎች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል በተለያዩ ወራቶች ከተገደሉት መካከል ዓስናቀውታፈረ፣  ሙሉጸሓይ፣ አቡሃይ ተክሌ ፣ ፣ ፈንታ አዛናው ፣ ድግሴ አድየ፣ ታደሰ ድረስ፣ ተስፋው አለሙ፣ ሙሉጌታ ማሞ፣ ደጀን

በይፋ፣ አለነ ተገኘ ፣ ሙላው አለሙ፣ ጋራ ጉርባ፣ ተስፋ፣ ዳርጌ አወቀ፣ ደጉ፣ ጨምር፣ ጥላሁን ፣ ሃብቴ አለምኔና ጸጋው ዘመነ የተባሉት ይገኙበታል።

ምህረት አባይ የተባለው ባለስልጣን ደግሞ እነ ሙላው አለሙን ማስገደሉን ነዋሪዎች ሲናገሩ፣ ሹመት የሚባለው የጎንደር የጸጥታ ሹም ደግሞ ከሳንጃ እስር ቤት በማስወጣት በእነ ደጉ፣ ጨምርና ጥላሁን ላይ እርምጃ ወስዷል።

በጉዳዩ ዙሪያ የወረዳዎችን አመራሮች  አስተያየት ለማካተት ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም።