በሳውድ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመውን የመብት ጥሰት ለመቃወም የሚደረጉ ሰልፎች እንደቀጠሉ ነው

ህዳር ፲፪(አስ ሁለት )ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሰኞ ኖቬምበር 25፤ 2013 ከ ጠዋቱ 8:30 ጀምሮ ሚድራንድ በሚገኘው ፓን አፍሪካ ፓርላማ ፊት ለፊት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያዘጋጁ ለኢሳት ተናግረዋል።

በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመገኘት ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ተማጽነዋል።