ሰማያዊ ፓርቲ በመጪው እሁድ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚካሄድ አስታወቀ

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ምንም እንኳ የአዲስ አበባ መስተዳደር ለሰልፉ  በ12 ሰአታት ውስጥ መልስ የመስጠት ሀላፊነት የነበረበት ቢሆንም ይህን አላዳረገም።  ፓርቲው የሚጠበቅበትን ሁሉ ለሚመለከተዉ አካል የማሳወቅ ግዴታ በአግባቡ ስለተወጣና ለሰልፉም የሚያስፈልጉ ስራዎች እየተከናወኑ በመሆኑ መስከረም 12 ቀን 2006 ዓ.ም በታቀደው መሰረት ሰልፉ ይካሄዳል ብሎአል፡፡ በዚህ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ የምናነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሲቪክ ...

Read More »

734 ሚሊዮን 600 ሺ ብር የመዘብሩ የስራ ሃፊዎች አለመቀጣታቸውን መረጃዎች አመለከቱ

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን የተገኝው መረጃ እንደሚያመለክተው ከተለያዩ የፌደራል መስሪያ ቤቶች 734 ሚሊዮን 6 መቶ ሺ ብር የመዘብሩ የስራ ሃፊዎች በተጣራ መረጃ ክስ ቢመሰረትባቸውም የውሳኔ ቅጣት እንዳልተላለፈባቸው ታውቋል። ለረጅም ጊዜ በተደረገ ምርመራ ተጣርቶና መስረጃ ተገኝቶባቸው ከ2004 ዓም ጀምሮ ክስ የተመሰረተባቸው የተለያዩ የሙስና ወንጀሎች የውሳኔ ሀሳብ እንዳልተላለፈባቸው ከመሰሪያ ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። በቤንሻንጉል ...

Read More »

የኢንዱስትሪው ዘርፍ የወጪ ንግድ አሽቆለቆለ

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ በኢንዱስትሪ ዘርፍ ባለፈው ዓመት የተመዘገበው የወጪ ንግድ (ኤክስፖርት) አፈጻጸም እጅግ አነስተኛ እንደነበር ከኢንዱስትሪ ሚ/ር የተገኘ መረጃ አመለከተ፡፡ በ2005 የኢትዮጵያዊያን በጀት ዓመት ከጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ ከቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ከአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ከፋርማሲዩቲካልስና ከኬሚካል የወጪ ንግድ 542 ሚሊዮን  4 መቶ ሺ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ ማሳካት የተቻለው 281 ሚሊዮን  2 መቶ ሺ  ዶላር ወይንም 52 በመቶ ያህሉን ብቻ ነው፡፡ ዘርፉን ባለፉት ሁለት ...

Read More »

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና ሌሎች በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ ተጠየቀ።

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ከዓመት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ለ14 ወራት በቃሊቲ እስርቤት ከታሰሩ በኋላ  ተፈተው የወጡት ስዊድናውያን ጋዜጠኞች  ማርቲን ሺቢ እና ዩዋን ፐርሹን እንዲሁም ዓለምዓቀፍ የሰብዓዊና የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተወካዮች፡ ጋዜጠኞችና በስዊድን የሚኖሩ በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እና ስዊድናውያን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባዘጋጀው ደብዳቤ ላይ ፊርማቸውን በማኖር  ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ  የታሰሩ ጋዜጠኞችን እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ኢትዮጵያ ውስጥ ያሳለፉትን የእስር ህይወት የሚተርከውን እና ...

Read More »

የአንበሶች መጋቢው -በአንበሳ መበላታቸው ተዘገበ።

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አዲስ አበባ በተለምዶ አንበሳ ግቢ ተብሎ በሚጠራው የአንበሶች ማቆያ ማእከል ውስጥ ዛሬ ከጠዋቱ 1:30 ላይ  የአንበሶች መጋቢ የነበሩ ግለሰብ በ አንበሳ መበለታቸውን ራዲዮ ፋና ዘገበ። እንደራዲዮጣቢያውዘገባአደጋው የተከሰተው   በዛሬው እለት ተረኛ ተንከባካቢ የነበሩት እና አቶ  አበራ ሲሳይ የተባሉትየአንበሶቹ መጋቢ፥ የአንበሶቹን ማዳሪያ እያጸዱ ባሉበት ወቅት ነው። ከጥንቃቄ ጉድለት ባልተዘጋው በር የገባውና  መጋቢውን ለህልፈተ ህይወት የዳረጋቸው አንበሳ ስሙ-ቀነኒሳ እንደሆነም ራዲዮው ጨምሮ ዘግቧል። የግለሰቡን ህይወት ለማትረፍ በወቅቱ በስራ ላይ የነበሩ የግቢው ሰራተኞች ጥረት ቢያደርጉም-ሳይሳካ መቅረቱንም ለማወቅ ተችሏል። የሟች አስከሬን ከመንከባከቢያ ስፍራው ወጥቶ ወደ ምኒሊክ ሆስፒታል ተወስዷል። የዚህ አይነት አደጋ  በ19 89 ዓ.ም መከሰቱ የሚታወስ ነው።

Read More »

አንድነት ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፉን ለመስከረም 19 ቀን 2006 ዓም አራዘመ

መስከረም ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፓርቲው የምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዘካርያስ የማነብርሀን እንደገለጹት የአዲስ አበባ መስተዳድር ከተማሪዎች ትምህርት መጀመር እና ከተለያዩ የአዲስ አመት በአላት ጋር በማያያዝ ፓርቲው ሰልፉን በሁለት ሳምንት እንዲያራዝም በተጠየቀው መሰረት፣ ጥያቄውን ተቀብሎ ለማራዘም ፈቃደኛ ሆኗል። መስተዳድሩ ፓርቲው ተቃውሞውን መስከረም 19 ማካሄድ የሚችል መሆኑን ከመስተዳድሩ ወረቀት አግኝቷል። አቶ ዘካሪያስ መስተዳድሩ ሰላማዊ ሰልፉን ለማራዘም የህግ ድጋፍ እንዳለው ገልጸው፣ ...

Read More »

ርእዮት አለሙ ምግብ ካቆመች 4ኛ ቀናትን ደፈነች

መስከረም ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እውቋ የብእር ሰው፣ የነጻነት ታጋይ፣ የዩኒስኮና የኢንተርናሽናል ውሜንስ  ሚዲያ ፋውንዴሽን አሸናፊ ጸሀፊና መምህርት ርእዮት አለሙ ዛሬም በረሀብ አድማው ገፍታበታለች። እህቷ እስከዳር አለሙ እንደገለጸችው ዛሬ እርሷና የርእዮት እጮኛ የሆነው ስለሺ ሀጎስ ወደ ቃሊቲ እስር ቤት ቢሄዱም እንዳይገቡ ተከልክለዋል። እጮኛዋ ስለሺ ለሰአታት ታግቶ በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች መደብደቡንም እስከዳር ተናግራለች  ርእዮት ከእናት፣ አበቷና የንስሀ አባታ በስተቀር ሌላ ...

Read More »

የስኳር ፋብሪካዎች የግንባታ ሂደት ችግር ውስጥ ነው ተባለ

መስከረም ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣዩ ዓመት በሚጠናቀቀው የአምስት ዓመት  ዕቅዱ በስኳር ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመገንባት ያቀደውን እንደማያሳካ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጹ። በህወሃት ነባር ታጋይ አቶ አባይ ጸሐዬ የሚመራው የስኳር ኮርፖሬሽን ከነባርና ዕውቀትና ልምዱ ካላቸው ባለሙያዎች ጋር ተግባብቶ መስራት ባለመቻሉ ብዙዎቹ ኮርፖሬሽኑንና በስሩ ከሚገኙ የስኳር ፋብሪካዎች ለቅቀዋል፡፡ ኮርፖሬሽን የገጠመውን የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ከውጪ አገር ባለሙያዎችን በመቅጠር ...

Read More »

ቻይና ለመለስ ፋውንዴሽን ማስገንቢያ ገንዘብ ለገሰች

መስከረም ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአቶ መለስን ፋውንዴሽን ለመገንባት መንግስትና የመለስ ፋውንዴሽን በጋራ በመንቀሳቀስ ላይ ባሉበት በዚህ ጊዜ፣ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ልኡካን ለፋውንዴሽኑ ግንባታ የሚውል 50 ሺ ዶላር ለመለገስ ቃል መግባቱዋን የልኡካን ቡድኑ መሪ ሚስተር ዛሆ ገልጸዋል። አቶ መለስ በቻይናና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር በማድረጋቸው  ልኢካኑ አመስግነዋቸዋል። ቻይና የኢትዮጵያን የአምስት አመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እንደምትደግፍም እኚሁ ባለስልጣን ገልጸዋል።

Read More »

የግብጽ ጊዜያዊ መንግስት የደነገገውን የ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ 2 ወራት አራዘመ።

መስከረም ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቢቢሲ  ከፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት የወጣውን መግለጫ በመጥቀስ እንደዘገበው፤  የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማራዘም ያስፈለገው  ከአገሪቱ የ ደህንነት ሁኔታ ጋር በተያያዘ ነው። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተደነገገው ባለፈው ነሐሴ ወር  በመሀመድ ሙርሲ ደጋፊዎች ላይ የግብጽ ፖሊስና መከላከያ የሀይል እርምጃ መውሰዳቸውን ተከትሎ ነው። የፕሬዚዳንት መሀመድ ሙርሲን ከስልጣን መወገድ በተቃወሙ ደጋፊዎቻቸው ላይ በተወሰደው እርምጃ  በመቶዎች የሚቆጠሩ ግብጻውያን መገደላቸው ይታወሳል። ...

Read More »