Amsterdam

አስር ሚሊዮን ዶላር ወይም 230 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የኢትዮጵያ በርበሬ ጥራቱን ያልጠበቀ ነው ተብሎ ከአውሮፖ ተመለሰ።

ግንቦት ፩ ( አንድ ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሳምንታዊው ካፒታል እንደዘገበው ከፍተኛ መጠን ያለው ይህ የተፈጬ በርበሬ ከአውሮፓ ገበያ ሊመለስ የቻለው፤ በአውሮፓ መግቢያ ባሉ ላቦራቶሪዎች በተደረገ ምርመራና ቁጥጥር አፍላቶክሲን እና ኦክራቶክሲን የተባሉ በካይ ንጥረ ነገሮች ስለተገኙበት ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ በርበሬው የተቀመጠውን የጥራት ደረጃ እስካላሟላ ድረስ ወደ ለንደን እንዳይገባ ባለፈው ዓመት የእንግሊዝ መንግስት እገዳ መጣሉ ይታወሳል። ይህም በመሆኑ ...

Read More »

የወጣት ሙጂብ አሚኖ የምስክርነት የድምጽ ፋይል ጠፋ በሚል ምክንያት የፍርድ ብያኔ ተራዘመ::

ግንቦት ፩ ( አንድ ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሕግ አግባብ ውጪ በእስር ሲንገላታ በቆየው በወጣት ሙጂብ አሚኖ ክስ ጉዳይ ዛሬ ግንቦት 1 ቀን 2009 ዓ.ም ያስቻለው የከፍተኛው ፍርድ ቤት ችሎት፤ የመከላከያ ምስክሮች ላይብይን ለመስጠት የተሰጠውን የጊዜ ቀጠሮ አራዘመ። ወጣት ሙጂቦ ፣በእነ ኤሊያስ ከድር የክስ መዝገብ በሃሰት አልመሰክርም በማለቱ፣ እንዲሁም በእነ ከድር መሃመድ የክስ መዝገብ የተከሠሱትን እነ አቡበከር ...

Read More »

ሞዛምቢክ 24 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ወደ አገራቸው መለሰች

ግንቦት ፩ ( አንድ ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሕገወጥ ቪዛ አስመትተው ከአዲስ አበባ ወደ ሞዛምቢኳ መዲና ማፑቶ የገቡ 24 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጋቸውን የአገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ። ከኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች በተጨማሪም 11 የባንግላዲሽ ዜጎችም በተመሳሳይ ሁኔታ በመግባታቸው እነሱም ወደ ትውልድ አገራቸው ተልከዋል። ኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች በማፑቶ አውራጃ በማቫሊ ድንበር አቆራርጠው ወደ ሞዛምቢክ መግባታቸውንም ባለስልጣኑ አክለው ገልጸዋል። ባለፈው ሚያዚያ ...

Read More »

በአፋርና አማራ ድንበሮች በተነሳ ግጭት ከ 15 በላይ ሰዎች ቆሰሉ

ሚያዝያ ፴ ( ሠላሳ ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት በአዳር ወረዳ ከባቲ 15 ኪ ሜ ርቀት ላይ በሚገኝ ቦታ ላይ ከድንበር ይገባኛል ጥያቄ ጋር በተያያዘ በተነሳ ግጭት ከ15 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ግጭቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት በአካባቢው የነበሩ የአጋዚ ወታደሮች ሁኔታውን ለማብረድ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አለማሳየታቸው ነዋሪዎችን ግራ አጋብቶአል ። እንደ ወረዳው ነዋሪዎች ገለጻ በአካባቢው ከዛሬ ...

Read More »

በስዊዘርላንድ የህወኃት አምባሳደር በመኖሪያ ቤታቸው የጠሩት ስብሰባ ተቃውሞ ገጠመው

ሚያዝያ ፴ ( ሠላሳ ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አምባሳደሩ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ለመወያዬት በሚል ነበር በመኖሪያ ቤታቸው የህወኃት- ኢህአዴግ አባላት የሆኑ ሰዎችን በምስጢር ስብሰባ የጠሩት። ስለ ጥሪው የሰሙ በስዊዘርላንድ የሚገኙ ሀገር ውዳድ ኢትዮጵያውያን “የሀገራችን ጉዳይ እኛንም ያገባናል” በማለት በቀጥታ ስብሰባው ወደተጠራበት ወደ አምባሳደሩ ቤት ሰተት ብለው ይገባሉ። ሁኔታው ስጋትና ጭንቀት ያሳደረባቸው የስብሰባው አስተባባሪዎች ልክ እንደ ጸጉረ ...

Read More »

የደህንነቱ መ/ቤት በአዲስ አበባ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሽብር ጥቃት ለማድረስ ማሴሩ ተሰማ

ሚያዝያ ፴ ( ሠላሳ ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፉት ወራት ውስጥ በጎንደርና በባህር ዳር ከአገዛዙ ጋር ቅርበት ባላቸው አካላት ላይ ያነጣጠሩ ተከታታይ ፍንዳታዎች ሲደርሱ ቆይተዋል። በጎንደር ከተማ በጥቂት ወራት ውስጥ ከአስር በላይ ፍንዳታዎች የተፈፀሙ ሲሆን፤ በእንግዶች ማረፊያ ሆቴል ላይ በደረሰ ፍንዳታ አንድ የውጭ ሃገር ዜጋን ጨምሮ አምስት ሰዎች እንደተጎዱ በወቅቱ መዘገባችን ይታወሳል። እንዲሁ በባህር ዳርም ጃሽን ቢራ ...

Read More »

የዶክተር አዲስ ዓለማዬሁን ሐውልት የመረቁት ሚኒስትር በቦታው የነበሩትን ታዳሚዎችን አሳዘኑ።

ሚያዝያ ፴ ( ሠላሳ ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፍቅር እስከመቃብርን ጨምሮ በርካታ ረዣዥምና ዘመን ተሻጋሪ ልቦለድ መጽሐፍትን ላበረከቱት ለታዋቂው ኢትዮጵያዊ ደራሲ ለክቡር ዶክተር ሐዲስ ዓለማዬሁ በደብረማርቆስ ከተማ የተገነባውን ሐውልት የመረቁት የባህል ሚኒስትሯ ወረቀታቸው ጠፍቷቸው ንግግራቸውን ማቋረጣቸው ተሰማ። ቅዳሜ ዕለት ሚያዚያ 28 ቀን 2009 ዓመተምህረት በተደረገው የመታሰቢያ ሐውልት ምርቃት ሥነ ስር ዓት ላይ የክብር እንግዳና ተናጋሪ የነበሩት ሚኒስትሯ ...

Read More »

76ኛው የድል በአል ተከብሮ ዋለ

ሚያዝያ ፳፯ ( ሃያ ሰባት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ይዘው ለመግዛት ባህር አቋርጠው የመጡትን የፋሽሽት ጣሊያን ወታደሮች፣ በአምስት አመት የአርበኝነት ተጋድሎ በማንበርከክ የኢትዮጵያን ነጻነት መልሰው እጃቸው ውስጥ ያስገቡበት፣ 76ኛው የድል በዓል በመላው ኢትዮጵያ ተከብሯል። አትዮጵያውያን አርበኞች በጎብዝ አለቆች እንዲሁም በጊዜው በነበሩ መሳፍንት እየተመሩ በዘመናዊ የጦር መሳሪያ ተደራጅቶ የመጣውንና መላ ኢትዮጵያን ወሮ ለመያዝ አልሞ የመጣውን ...

Read More »

በደንቢያ የተጠራው ስብሰባ ተቃውሞ ገጠመው

ሚያዝያ ፳፯ ( ሃያ ሰባት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የተለያዩ ተቃውሞዎችን ስታስተናገድ በከረመችው ደንቢያ፣ የተጠራው ስብሰባ ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞ እንደቀረበበትና ስብሰባው ተቋርጦ እንደነበር ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። የወረዳው አስተዳደር ዘይት እናከፋፍላለን በማለት ህዝቡ በስብሰባው ላይ እንዲገኝ ያደረገ ቢሆንም፣ የዘይት ችግር የሚለው አጀንዳ ተለውጦ ስለሰላም እና ስለጸጥታ ንግግር በሚደረግበት ወቅት፣ ህዝቡ “ ዘይት ብላችሁ ነው የጠራችሁን፣ አሁን የምታወሩን ...

Read More »

ክፍያ ቢፈጽሙም የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁንን የሙዚቃ አልበም እንዳይሸጡ መከልከላቸውን ነጋዴዎች ተናገሩ

ሚያዝያ ፳፯ ( ሃያ ሰባት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በባህርዳር እና ጎንደር ከተማ የሚገኙ ነጋዴዎች እንደገለጹት የዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ “ኢትዮጵያ” የሚለው አዲሱ የሙዚቃ ስራው በመኪኖች ላይ እየተዞረ እንዳይሸጥ ተከልክሏል። ነጋዴዎቹ “በአዲስ አበባ እንጅ በዚህ አካባቢ እንድትሸጡ ፈቃድ አልተሰጣችሁም” ከተባሉ በሁዋላ የማከፋፈል ፈቃድ ሲጠይቁ ከአንዱ መስሪያ ቤት ወደ ሌላው በማመላለስ ሊሳካላቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል። የቅስቀሳ ስራ ለመስራት በቀን ...

Read More »