የካቲት ፫(ሦስት) ቀን፳፻፯ዓ/ምኢሳትዜና :-መጪውን ምርጫ ተከትሎ እያንዳንዱን መራጭ የሚቆጣጠርበትን ፎርም አዘጋጅቶ ለአባላቱ በድብቅ ያሰራጨው ኢህአዴግ፣ እያንዳንዱ አባል ከምርጫ ቦርድ የተመዝጋቢውን ስም ዝርዝር በመውሰድ ስለመራጩ ባህሪ፣ የፖለቲካ አቋምና ብሄር በዝርዝር ሞልቶ እንዲያስረክብ ያዛል። የዚሁ ፎርም ቅጅ ኢሳት እጅ የገባ ሲሆን፣ ፎርሙ መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያ ከመሄዳቸው በፊት ኢህአዴግ አስቀድሞ የሚቆጣጠርበትን መንገድ ያመቻችለታል፡፡ የኢህአዴግ ካድሬዎች የመራጩን ማንነት ካወቁ በሁዋላ የአካባቢ ሹሞች ወደ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እናት ልጃቸውን ማዬት ይችሉ ዘንድ እንዲፈቀድላቸው የተማጽኖ ደብዳቤጻፉ።
የካቲት ፫(ሦስት) ቀን፳፻፯ዓ/ምኢሳትዜና :-ወ/ሮፋናዬእርዳቸውትናንትየካቲት 2 ቀን 2007 ዓመተ ምህረት ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን በጻፉት ደብዳቤ፤ሀሳቡንበጽሁፍበመግለጹየሶስትአመትእስራትተፈርዶበትበእስርላይበሚገኘውልጃቸውላይ፤ቤተሰቦቹንጨምሮበማንምሰውእንዳይጎበኝየተጣለበትእገዳእንዲነሳለትናእርሳቸውምየልጃቸውንዓይንማዬትይችሉሰንድእንዲፈቀድላቸውአቤትብለዋል። <<መቼም፣የእናትሆድአያስችልምናእባካችሁልጄንታደጉት፡፡እባካችሁቢያንስካለበትእየሄድኩየልጄንአይንእንዳይእንዲፈቀድልኝተባበሩኝ፡፡የልጄንድምጽከሠማሁይኸዉአንድወርሞላኝ፡፡>>ብለዋልወ/ሮፋናዬ በደብዳቤያቸው። <<ታናሽወንድሙታሪኩደሳለኝለወንድሙብሎየያዘውንምሣለማድረስዝዋይማረሚያቤትቢሄድምበማረሚያቤቱጠባቂዎችተደብድቦየያዘውንምግብሣያደርስሜዳላይተደፍቶተመልሷል፡፡>> ያሉትየተመስገንእናት፤ <<መቼምእናንተምልጆችይኖራችኋል፤ደግሞምየልጅንነገርታውቁታላችሁ፡፡እኔአሁንበእርጅናዕድሜዬላይእገኛለሁ፡፡ከአሁንበኋላብቆይምለትንሽጊዜያትነው፡፡በዚህችጊዜውስጥልጄንእየተመላለስኩእየጠየኩ፣ድምፁንእያሰማሁ፣አይዞህእያልኩብኖርለእኔመታደልነበር፡፡እባካችሁእርዱኝየልጄድምጽናፈቀኝ፡፡>> ብለዋል። <<ተምዬስታመምየሚያስታምመኝ፣ “አይዞሽእማዬ” የሚለኝረዳቴነው፡፡ሌላዘመድየለኝም፡፡>>ያሉትወ/ሮፋናዬ <<የምተዳደረውምልጆቼለፍተውናደክመውበሚያመጧትትንሽብርነበር፡፡ዛሬግንይኸዉልጆቼምወንድማቸውንለማየትእየተንከራተቱነው፡፡>>ብለዋል። እኔምንምአቅምየሌለኝአሮጊትነኝ፡፡ሁሉንምለናንተሠጥቻችኋለሁ፡፡ከእግዚአብሄርጋርእንደምታስተካክሉልኝእናእንደገናየልጄንፊትእንዳይእንደምታደርጉኝሙሉተስፋአለኝ ያሉት የተመስገን እናት፣ ደብዳቤውንለሰብአዊመብትኮሚሽንበግልባጭ ደግሞ ለጠ/ሚኒስተርፅ/ቤት፣ለምክርቤቱየህግና፣ፍትህናአስተዳደርጉዳዮችቋሚኮሚቴ፣ለአፈ-ጉባኤፅ/ቤት፣ለሰብዓዊመብቶችጉባኤ (ሰመጉ)፣ለእምባጠባቂ፣ለአሜሪካኢምባሲእናለእንግሊዝኢምባሲ አሳውቀዋል።
Read More »እንዲከላከሉብይንተላልፎባቸውየነበሩትየሰማያዊፓርቲአባል ከእስርተፈቱ
የካቲት ፫(ሦስት) ቀን፳፻፯ዓ/ምኢሳትዜና :-በ9ኙፓርቲዎችትብብርየአዳርሰልፍ ወቅት <<በራሪወረቀትበትነሃል >>ተብለው ካለፈውህዳር 24 ጀምሮበእስርየሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲአባልአቶሲሳይዘርፉየ 2 ወርከ10 ቀን ተበይኖባቸው ነበር። በፖሊስመያዛቸውንተከትሎ ‹‹የመንግስትንስምበማጥፋት›› ክስየተመሰረተባቸውአቶሲሳይ፤ጉዳያቸውንሲመለከተውበነበረውፍርድቤትከሳምንታትበፊትየጥፋተኝነትብይንእንደተላለፈባቸውይታወሳል። አቶሲሳይበፖሊስከተያዘበትህዳር 24 ቀን 2007 ዓ.ምጀምሮዋስትናተከልክለውበእስርላይበመቆየታቸውታሳቢሲደረግ የቅጣትውሳኔያቸውንስለጨረሱከእስርእንዲፈቱትዕዛዝተሰጥቷል፡፡
Read More »በአማራና ትግራይ ድንበር የተነሳውን ውዝግብ ለመፍታት የተጠራው ስብሰባ ተበተነ
ጥር ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራና በትግራይ ክልል ድንበሮች አካባቢ የተነሳውን ችግር ለመፍታት ከፌደራል መንግስት ፣ ከትግራይና ከአማራ ክልል የተውጣጡ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ጥር 26 ቀን 2007 ዓም ከሁለቱም ክልሎች የተውጣጡ 300 ነዋሪዎችን ሰብስበው ያነጋገሩ ቢሆንም፣ መግባባት ሳይቻል በመቅረቱ ለየካቲት 4 በድጋሜ መቀጠሩን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል። የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ሽፈራው ተክለማርያም፣ የአማራ ክልል ፕ/ት ገዱ አንዳርጋቸው፣ የትግራይ ክልል ...
Read More »በአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጥሰት ዙሪያ መከረ
ጥር ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህብረቱ ጥር 27፣2007 ዓም በብራሰልስ ቤልጂየም የአውሮፓ ህብረት ጽ/ቤት ውስጥ ለ3 ሰአታት ባደረገው የኢትዮጵያ የሰአብአዊ መብት ግምገማ በኦጋዴን ክልል እና በተቀሩት የኢትዮጵያ ግዛቶች በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ሰቆቃ የአውሮፓ ህብረትና አባል መንግስታት በዝምታ መመልከታቸውን ማብቃት አለበት የሚል ውሳኔ አስተላልፈዋል። ስብሰባውን ያዘጋጁት የህብረቱ የሶሻሊስትና የዲሞክራቲክ ፓርቲዎች ጥምር ህብረት ፣ ውክልና አልባ ህዝቦች ተቆርቋሪ ...
Read More »ከሰራተኞች ጋር የተካሄደ ስብሰባ ያለስምምነት ተጠናቀቀ
ጥር ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በስብሰባው የተካፈሉ የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት፤ላለፉት ሁለት ቀናት ከኮርፖሬሽኑ ሰራተኞች ጋር በተደረገው ስብሰባ ኪራይ ሰብሳቢነት ወይም ጥቅመኝነት ፣ብሄራዊ ጥቅምን አሳልፎ መስጠት እና ሴኩሪቲ ክሊራንስ የሚሉ አጀንዳዎች ተነስተው ውይይት የተደረገባቸው ቢሆንም፣ ስምምነት ሳይደረስባቸው ቀርቷል። የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ የኢንዱስትሪ አመራራሮች ሰራተኛውን፦መረጃ ወደ ውጭ አውጥታችሁ ትሰጣላችሁ፣ የሜቴክ ማለትም የኮርፖሬሽኑ እቃ አይረባም እያላችሁ ታወራላችሁ፣ ደሞዛችን ትንሽ ነው እያላችሁ ...
Read More »መንግስት በፌስ ቡክና በሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች ያሰማራቸው ሰዎች የተፈለገውን ውጤት ማምጣት አልቻሉም ተባለ።
ጥር ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ማህበራዊ ድረገጾች ላይ የመንግስትን መልካም ገጽታ ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊደርጉ ይችላሉ በሚል ተከታታይ ስልጠና ተሰጥቷቸው የነበሩት የህዝብ ግንኑነት ባለሙያዎች (ኮምኒኬተሮች) እና የመንግስት ባለስልጣናት፤የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አልቻሉም መባላቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖ ጠቆሙ፡፡ ለመንግስት የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎችና ለካድሬዎች በአቶ ሬድዋን ሁሴን በሚመራው የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት አማካይነት ከአራት ወር በፊት በማህበራዊ ድረገጾች አጠቃቀምና በመንግስት ...
Read More »ጸሃፊ አቤል ዋቤላ በእስር ቤት ስቃይ እንደደረሰበት ተናገረ
ጥር ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሰው ለወራት በእስር ቤት የሚሰቃዩት ዞን ዘጠኝ እየተባሉ የሚጠሩት ጋዜጠኞችና ጸሃፊዎች ዳኛ ይቀየርልን የሚል ማመልከቻ ማቅረባቸውን ተከትሎ ፣ ጉዳዩን ለማየት በተሰየመው ችሎት፣ ወጣቱ ጸሃፊ አቤል ዋቤላ በእስር ቤት ውስጥ የደረሰበትን ግፍ ተናግሯል። አቤል ከፍርድ ቤት ወደ እስር ቤት በሚመለስበት ወቅት እጅህ በሰንሰለት ለምን አልታሰረም በሚል ሰበብ ሌሊቱን ሙሉ እጆቹን በውሻ ...
Read More »ታሪካዊው “መስቀል ፍላወር” ሆቴል እንዲፈርስ ተወሰነ
ጥር ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፎርቹን ሳምንታዊ ጋዜጣ እንደዘገበው፤ ሆቴሉ የሚፈርሰው በአካባቢው ለሚሰራ የ 3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ ፕሮጀክት ተብሎ ነው። የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገዷን ለመስራት 400 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል መባሉንም ጋዜጣው አስነብቧል። ሆቴሉ ለልማት ፕሮግራም ተብሎ እንዲፈርስ ከአስር ቀን በፊት በቂርቆስ ክፍለ-ከተማ ትዕዛዝ መውጣቱ ተመልክቷል። ባለፈው ስርዓት የመንግስት እንዲሆን ተደርጎ በዋቢ ሸበሌ ሆቴሎች ...
Read More »ለህውሃት 40ኛ አመት መታሰቢያ ድግስ ከባለሀብቶች ብቻ 45 ሚልየን ብር ተገኘቷል፡፡
ጥር ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ(ህወሀት) ጽ/ቤት በተሰጠው መግለጫ እንደተመለከተው፤ የካቲት 11 ለሚከበረው የድርጅቱ 40ኛ ዓመት በዓል ማክበሪያ ከባለሀብቱ ብቻ 45 ሚልዩን ብር ስፖንሰር ተገኝቷል፡፡ በመግለጫው በመቀሌ ከፍተኛ ተራራ ላይ የመለስን ምስል የያዘ ባለሁት አውታር ሐውልት እየተገነባ እንደሆነ የተጠቀሰ ሲሆን፤ የዚህም ወጪ ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ አና ከገጠር መንገዶች ተቋራጭ ድርጅት ይሸፈናል ተብሏል፡፡ እስካሁን በአዲስ አበባ ...
Read More »