.የኢሳት አማርኛ ዜና

በቢሾፍቱ (ደብረዘይት) በአንድ ሆቴል ውስጥ የተወረወረ ቦንብ ጉዳት አደረሰ

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2008) በቢሾፍቱ ወይንም ደብረዘይት ከተማ በዛሬው ዕለት መጋቢት 22/2008 በአንድ ሆቴል ላይ በተወረወረ የእጅ ቦንብ በሰዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ታወቀ። በቦምቡ በትንሹ አንድ ህጻን መገደሉት የአይን እማኞችና የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል። በቢሾፍቱ ጥበቃውም ተጠናክሮ መቀጠሉም ተመልክቷል። አዋሽ በተባለ ሆቴል ላይ ማንነቱ ባልታወቀ ግለሰብ በተወረወረ የእጅ ቦምብ የሶስት ዓመት ህጻን  የተገደለ ሲሆን፣ የህጻኑ ወላጆችም መቁሰላቸውም ታውቋል። ...

Read More »

የስፔይ ኩባንያ በኢትዮጵያ የቆላ ዝምብ በሽታን ለመከላከል ሰው አልባ አውሮፕላን ሊጠቀም ነው

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2008) አንድ የስፔን ኩባንያ ሰው አልባ አውሮፕላኖች በመጠቀም በቆላ ዝንቦች አማካኝነት የሚመጣውን የእንቅልፍ በሽታ በማይራቡ የቆላ ዝምቦች ለመከላከል እንደሚቻል ገለጸ። የእንስሳት ደም የሚመገበው የቆላ ዝምብ፣ በሰዎች ላይ የድካምና ትኩሳት መለያ ባህርይ ያለው የእንቅልፍ በሽታ እንደሚያመጣና፣ በጊዜው ህክምና ካላገኘ በሰውና በእንስሳት ላይ ሞት ሊያስከትል እንደሚችል ተነግሯል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ባሉት አገራት በብዛት የሚገኘው የቆላ ዝምብ፣ በየአመቱ ...

Read More »

በኦሮሚያ ከተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ በኋላ የኢንቨስትመንት ፍላጎት ጨምሯል ሲሉ አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ገለጹ

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2008) በኦሮሚያ ከተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያየዘ በአጠቃላይ የወደመው ንብረት ከመቶ ሚሊዮን ብር ስለማይበልጥ ብዙ ጉዳት አልደረሰም ሲሉ አቶ ሃይለማሪያ ደሳለኝ ገለጹ። ጠ/ሚኒስትር ሃይለማሪያም ይህንን የተናገሩት ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲሆን፣ በጸጥታ ሃይሎች ስለተገደሉ ሟቾች እንዲሁን ታጣቂዎች ዘረፋ ተፈጸመብን ስላሉት ወገኖች አስተያየት አልሰጡም። በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ በቀጣዩ በሃገሪቱ ኢንቨስትመንት ላይ የሚያመጣውን ጉዳት በተመለከተ ...

Read More »

የአሜሪካ ልዑካን በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ በተመለከተ ማብራሪያ ጠየቁ

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2008) በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ለመመልከትና ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ለመምከር ወደኢትዮጵያ የተጓዘው የአሜሪካ መንግስት ከፍተኛ ልዑካን በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ያሉ ግጭቶችን ጨምሮ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ባለው የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ማብራሪያ ጠየቁ። በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲሞራሲያ የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ሚኒስቴር ቶም ማሊኖዊስኪ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የአሜሪካ አምባሳደር ፓትሪሺያ ሃስላክ ጋር በመሆን፣ ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ...

Read More »

የመሃመድ አልአሙዲን ሆራይዘን እርሻ ሃላፊነቱ የግል ማህበር ግማሽ ቢሊዮን ብር ቅጣት ተጣለበት

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2008) የቢሊኒየሩ ባለሃብት የሼህ መሃመድ አላሙዲን ንብረት የሆነው ሆራይዘን እርሻ ሃላፊነቱ ይተወሰነ የግል ማህበር ግማሽ ቢሊዮን ብር ቅጣት ተጣለበት። ገንዘቡም ለማህበራዊ አገልግሎት መስሪያ ቤት ገቢ እንዲደረግ ውሳኔ ተላልፏል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ተዘዋዋሪ ከፍተኛ ችሎት የመሃመድ አልአሙዲን ንብረት በሆነው ሆራይዘን እርሻ ሃላፊነቱ የግል ማህበር ላይ ቅጣቱን የወሰነው ከመንግስት የልማት ድርጅቶች ለፈጸመው ግዢ ክፍያ ባለመፈጸሙ እንደሆነ ...

Read More »

እነ አቶ አለማየሁ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጠባቸው

መጋቢት ፳፪( ሃያ ሁለት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የህወሃት ኩባንያዎችና አባላት በደቡብ አሞ ዞን ከፍተኛ መሪዎች መውሰዳቸው ከተጋለጠ በሁዋላ በቁጥጥር ስር የዋሉት የደቡበ አሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት ም/ሊቀመንበርና የዞኑ ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ አቶ ዓለማየሁ መኮንን፣ የፓርቲው አባል አቶ አብረሃም ብዙነህ እንዲሁም አቶ ስለሺ ጌታቸው ከጅንካ እስር ቤት ወደ አዋሳ እስር ቤት እንዲዛውሩ ከተደርጉ በሁዋላ ረቡእ ክሰአት በሁዋላ ...

Read More »

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም አምባሳደሮችን እየተማጻኑ ነው

መጋቢት ፳፪( ሃያ ሁለት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የህወሃቱ አመራር አባልና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም ለተመድ የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርነት ቦታ ለመወዳደር የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችን መንግስታቸውን አሳምነው ድጋፍ እንዲሰጡ ያደርጉላቸው ዘንድ በመማጸን ላይ መሆናቸው ታውቁዋል። ሰሞኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የአፍሪካና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራትን አምባሳደሮች መንግስቶቻቸው በምርጫው ድጋፋቸው እንዲሰጡዋቸው ያደርጉላቸው ዘንድ ሲማጸኑ ...

Read More »

በአዲስ አበባ ሕጻናት በምግብ እጥረት ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደዱ

በአዲስ አበባ በምግብ እጥረት ምክንያት ትምህርት የሚያቋርጡ እና ውጤታማ መሆን ያልቻሉ ልጆች ቁጥር እያሻቀበ ነው። የትምህርት ቤቶችን ቁጥር በመጨመር ሕፃናት በነፃ ትምህርት የሚያገኙበት እድል ቢመቻችም፣ በቂ ምግብ አለማግኘታቸው ተከትሎ ብዙዎችን ከትምህርት ገበታቸው እያፈናቀላቸው መሆኑ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። ባለፈው ዓመት ከበጎ አድራጊ መንግስታዊ ካልሆኑ ግብረሰናይ ድርጅቶች በትምህርት ቤት ምግብ ይቀርብላቸው የነበሩት ሕጻናት፣ አምስት ሺህ ነበሩ። በምግብ እጦትና ቤተሰብ ገቢ ...

Read More »

አራቱ የሚድሮክ ኢትዮጵያ ድርጅቶች ግማሽ ቢሊዮን ብር እንዲከፍሉ ተፈረደባቸው

መጋቢት ፳፪( ሃያ ሁለት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአራት የኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙት ባለቤትነታቸው በሚድሮክ ስር የሚገኙት ጎጀብ አግሪካልቸር፣ ሆሪዞን አዲስ ታየር፣ ሊሙ ኮፊ ፋርምና በበቃ የቡና ማቀነባበሪያ ድርጅቶች ለፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ግማሽ ቢሊዮን ብር እንዲከፍሉ ሲል ፍርድ ቤቱ በይኗል። ፍርድ ቤቱ እነዚህ አራቱ ድርጅቶች ወደ ሚድሮክ በሚዘዋወሩበት ወቅት በቅድሚያና በተወሰነ ክፍያ መክፈል የነበረባቸውን ክፍያዎች ...

Read More »

ወደታንዛኒያ የሚገቡ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 21 ፥ 2008) የታንዛኒያ መንግስት ከኢትዮጵያ በህገወጥ መንገድ ወደሃገሩ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ረቡዕ አስታወቀ። ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ ሃገሪቱ በህገወጥ መንገድ መግባታቸውን ያስታወቀው የታንዛኒያ ፖሊስ በተያዘው ሳምንት ተጨማሪ ስድስት ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል። ወደሃገሪቱ በህገወጥ መንገድ ገብተዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያንም ከነገ በስቲያ አርብ ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ እንደሚመሰረትባቸው ዘ-ጋርዲያን የተሰኘ የታንዛኒያ ...

Read More »