.የኢሳት አማርኛ ዜና

አንድ እስራዔላዊ የግርዛት ባለሙያ ተማሪዎቻቸው በኢትዮጵያና በሱዳን ህጻናት ላይ ልምምድ እንዲያካሄዱ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተጋለጠ

ኢሳት (ህዳር 21 ፥ 2009) በእስራዔል አገር የግርዛት ትምህርትን በመስጠት የሚታወቁት አንድ የሃገሪቱ አንጋፋ ባለሙያ ትምህርት የሚሰጧቸው በርካታ ተማሪዎች በኢትዮጵያና በሱዳን ህጻናት ላይ ልምምድ እንዲያካሄዱ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተጋለጠ። የሃገሪቱ የህክምና ባለሙያዎች በበኩላቸው በአንድ ታዋቂ የምርመራ ጋዜጠኛ በድብቅ የተደረገው የቪዲዮ ቃለ-ምልልስ ተግባራዊ ሆኖ ከሆነ ድርጊቱ እጅት አስደንጋጭና አሳዛኝ ነው ሲሉ አስታውቀዋል። በዘርፉ የ33 አመት የስራ ልምድ ያላቸው መምህሩ ኤሊያሁ አሱሊን የእስራዔሉ ...

Read More »

የገዳ ስርዓት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) የአለም ወካይ ቅርስ ተደርጎ ተመዘገበ

ኢሳት (ህዳር 21 ፥ 2009) የኦሮሞ ህዝብ ባህላዊ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር የሆነው የገዳ ስርዓት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) የአለም ወካይ ቅርስ ተደርጎ ተመዘገበ። በአዲስ አበባ ከተማ አመታዊ ጉባዔውን እያካሄደ የሚገኘው ድርጅቱ ከገዳ ስርዓት በተጨማሪ የ10 ሃገራት ወካይ ቅርሶች የማይዳሰዱ ቅርሶች ሆነው እንዲመዘገቡ ማድረጉን በሃገር ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን ረቡዕ ዘግበዋል። የገዳ ስርዓት በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ዴሞክራሲንናና ሰላማዊ ...

Read More »

በደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢዎች የተከሰተው ድርቅ ወደ አጎራባች ክልሎች መዛመቱ ስጋት እንደፈጠረ ተመድ አስታወቀ

ኢሳት (ህዳር 21 ፥ 2009) በደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢዎች የተከሰተው አዲስ የድርቅ አደጋ ወደ አጎራባች ክልሎች በመዛመት ስጋት ማሳደሩን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረቡዕ አስታወቀ። በሶማሌ፣ አፋር፣ ኦሮምያና ደቡብ ህዝቦች ስር የሚገኙ በርካታ ዞኖች ካለፈው ወር ጀምሮ በአካባቢው በተከሰተ አዲስ የድርቅ አደጋ ለሰብዓዊ እርዳታ መጋለጣቸው ይፋ መደረጉ ይታወሳል። ይኸው አዲስ የድርቅ አደጋ በሰሜን ምስራቅ የአማራ ክልል እንዲሁም በአንዳንድ የደቡብ የትግራይ ዞኖች ...

Read More »

የውጭ ባለሃብቶች ከሃገር ውስጥ ባለሃብቶች እኩል ብድር የሚያገኙበት ሁኔታ እንዲመቻች የብድር ፖሊሲ እንዲከለስ ትዕዛዝ ተላለፈ

ኢሳት (ህዳር 21 ፥ 2009) የኢትዮጵያ ወጪ ንግድ መቀነስን ተከትሎ መንግስት የውጭ ባለሃብቶች ከሃገር ውስጥ ባለሃብቶች እኩል ብድር የሚያገኙበት ሁኔታ እንዲመቻች የብድር ፖሊስ በድጋሚ እንዲከለስ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ተገለጸ። በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቅርቡ ያልስተላለፈውን ውሳኔ በመሻር በተለይ በአበባና ፍራፍሬ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከሃገር ውስጥ ባለሃብቶች እኩል ብድር እንዲያገኙ እንዲደረግ ውሳኔን መሰጠቱን በሃገር ውስጥ ያሉ ...

Read More »

በሱዳን የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል ተባለ

ኢሳት (ህዳር 21 ፥ 2009) ሰሞኑን ከሸቀጣ-ሸቀጦች ዋጋ መናር ጋር በተገናኘ በሱዳን የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ተጠናክሮ ቀጠለ። በተማሪዎች ተጀምሮ የነበረው ይኸው ተቃውሞ ረቡዕ የህግ ባለሙያዎችን በማቀፍ በሱዳን መንግስት የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንዲቆሙ የሚጠይቅ ትዕይንት በመዲናይቱ ካርቱም ረቡዕ ለሁለተኛ ጊዜ ሲካሄድ መዋሉን ቢቢሲ ዘግቧል። ከቀናት በፊት የሃገሪቱ ተማሪዎች መንግስት በነዳጅ ምርት ላይ ሲያደርግ የነበረው ድጎማ መነሳት ...

Read More »

በሰሜን ጎንደር በነጻነት ሃይሎች እና በአገዛዙ ወታደሮች መካከል የሚካሄደው ጦርነት ቀጥሎ ዋለ

ኅዳር ፳ (ሃያ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአካባቢው ምንጮች እንደገለጹት በነጻነት ሃይሎች እና በገዢው ፓርቲ ወታደሮች መካከል ለሳምንታት የዘለቀው ጦርነት ዛሬ በደቡብ ጎንደርና በበለሳ መሃከል ዳዊጭ በሚባል አካባቢ ቀጥሎ ውሎአል። በሁለቱም ወገኖች ስለደረሰው ጉዳት ዝርዝር መረጃ አልደረሰንም። ይሁን እንጅ ጦርነቱ ከፍተኛ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል። በሌላ በኩል አገዛዙ ሰራዊቱን ወደ ተለያዩ አካባቢዎች እያንቀሳቀሰ ሲሆን ፣ ትናንት ሰኞ ወታደሮችን የጫኑ ኦራል ...

Read More »

የጎንደር ማረሚያ ቤት ሃላፊ ታሰሩ

ኅዳር ፳ (ሃያ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ካለፈው አርብ ጀምሮ በቁጥጥር ስር የሚገኙት ኢንስፔክተር ልጃለም መሰረት የታሰሩት ከኮሎኔል ደመቀ ዘውዴ ጋር በተያያዘ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። ኢንስፔክተሩ ባለፈው አርብ ኮሎኔል ደመቀ ፍርድ ቤት ቀርበው በነበረበት ወቅት እጃቸው በካቴና ሳይታሰር እንዳይቀርቡ አድርገዋል በሚል ነው። ኢንስፔክተሩ እስካሁን ደረስ ፍርድ ቤት አልቀረቡም። የአካባቢው ፖሊሶች የኢንስፔክተሩን መታሰር አጥብቀው እየተቃወሙት ነው።

Read More »

በኬንያ ቱርካና ሃይቅ ዳርቻዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች እየተሰደዱ ነው

ኅዳር ፳ (ሃያ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሰሜናዊ ምዕራብ ኬንያ በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ዜጎች ቁጥራቸው ከ10 ሽህ በላይ የሚሆኑ ቤተሰቦች መኖሪያ ቀያቸውን በመተው ወደ ኡጋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ተሰደዱ። የአካባቢው ነዋሪዎችን ለስደት ያበቃቸው ለከብቶቻቸው የግጦሽ ፣ ለምግብ እና የመጠጥ ውሃ  ፍለጋ ሲሆን በድርቁ ምክንያት ከአንድ ሺህ በላይ የቤት እንስሳት ሞተዋል። ተፈናቃዮቹ በኡዳንዳ ከፍተኛ ተግዳሮቶች እንደተደቀኑባቸው ሲቲዝን ...

Read More »

ዓርበኞች ግንቦት 7 በለንደን በተሳካ ሁኔታ ሕዝባዊ ስብሰባውን አካሄደ

ኅዳር ፳ (ሃያ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዓርበኞች ግንቦት 7 በእንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን ውስጥ ሕዝባዊ ስብሰባውን  እ.ኤ.አ. ኖቨንበር 27 ቀን 2016 በድምቀት አካሄደ። በስፍራው ላይ የአፍሪካ ኢንስቲቱት ሴኩሪቲ ስተዲስ ዳሬክተር የሆኑት የተከበሩ ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ፣ ሚስ ካትሪን ፕሉየር በለንደን ዩናይትድ ኔሽን አሶሴሽን የሳውዝ ኢስት ሪጅን ዳሬክተር እና የዓርበኞች ግንቦት 7 ከፍተና አመራር አባል አቶ ብዙነህ ጽጌ በስብሰባው ላይ ...

Read More »

የብሪታኒያ ሌበር ፓርቲ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲፈቱ ለሃገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ጥሪ አቀረበ

ኢሳት (ህዳር 20 ፥ 2009) የብሪታኒያው አዲሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ለሃገሪቱ  ዜጎች መብት መከበር የገቡትን ቃል በማክበር አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹ የሃገሪቱ ሌበር ፓርቲ ጥሪውን አቀረበ። በአቶ አንዳርጋቸው ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክቶ መግለጫን ያወጣው ፓርቲው፣ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉዳዩን ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲከታተሉ ለማድረግ የፊርማ ድጋፍ የማሰባባሰቢያ ዘመቻ እንደሚያካሄዱም ይፋ አድርጓል። ላለፉት ሶስት ወራት የብሪታኒያ ባለስልጣናት አቶ ...

Read More »