.የኢሳት አማርኛ ዜና

ሰሜን ኮሪያ የአገሪቱን መሪ ኪም ጆን ኡንን በባዮ-ኬሚካል ንጥረ ነገር በመመረዝ ለመግደል የታቀደው ሴራ መክሸፉ ገለጸች

ኢሳት (ሚያዚያ 26 ፥ 2009) የግድያ ሴራውን አስመልክቶ የሰሜን ኮሪያ የመንግስት ዜና አገልግሎት ድርጅት እንደገለጸው፣ በሰሜን ኮሪያ በህቡዕ የሚሰራ አሸባሪ ሃይል ከአሜሪካው የስለላ ድርጅት (CIA)ና ከደቡብ ኮሪያ የጸጥታ አገልግሎት (IS) ጋር በመተባበር ጥቃቱን ለመፈጸም አቅደው እንደነበር ገልጿል። የሰሜን ኮሪያ የዜና አገልግሎቱ በታላቁ መሪ ማለትም ኪም ጆን ኡንን ላይ ታቅዶ ስለነበረው የመግደል ሙከራ የሰጠው ምንም አይነት ተጨባጭ መረጃ ባይኖርም፣ ሴራው በቅርብ ...

Read More »

የአቶ አሰፋ ጫቦ የቀብር ስነስርዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈጸመ

ኢሳት (ሚያዚያ 27 ፥ 2009) የታዋቂው የህግ ባልሙያ፣ ፖለቲከኛና ጸሃፊ አቶ አሰፋ ጫቦ የቀብር ስነስርዓት ሚያዚያ 2009 አም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈጸመ። ለ25 አመታት በአሜሪካ ስደት ላይ የነበሩት አቶ አሰፋ ጫቦ በሚኖሩበት ዳለስ ቴክሳስ ግዛት በ75 አመታቸው በቅርቡ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል። አቶ አሰፋ ጫቦ የኢትዮጵያ ጭቁን አብዮታዊ ትብብር (ኢጭአት) ፓርቲ መስራችና ሊቀመንበር በመሆን በደርግ ጊዜ የታወቁ ...

Read More »

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች በአሜሪካ ያለክፍያ የመውለድ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን የአሜሪካ ኤምባሲ ገለጸ

ኢሳት (ሚያዚያ 26 ፥ 2009) በኢትዮጵያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ለጉብኝት በሚል ወደ አሜሪካ በመሄድ ያለምንም ክፍያ የመውለድ አገልግሎት ማግኘታቸው ስጋት እንዳሳደረበት ገለጸ። ኤምባሲው ለአየር መንገዱ ባቀረበው አቤቱቷ ወደ አሜሪካ በተለያዩ ጊዜያት ተጉዘው ማንኛውንም ህክምና ያደረጉ ሰራተኞችን በተመለከተ ሪፖርት እንዲያደርጉለት ጥያቄ ማቅረቡን አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል። ኤምባሲው ለእረፍት በሚል ወደ ሃገሪቱ ሄደው የመውለድ እና የተለያዩ አገልግሎት ያገኙ ...

Read More »

የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከሶስት ወር ያነሰ የገቢ ሸቀጦችን ወጪ ብቻ ለመሸፈን የሚያስችል መሆኑ ተመለከተ

ኢሳት (ሚያዚያ 27 ፥ 2009) የብሄራዊ ባንክ የሃገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከሶስት ወር ያነሰ የገቢ ሸቀጦችን ወጪ ብቻ ለመሸፈን የሚያስችል መሆኑን የባንኩ አረጋገጠ። በአስመጪ ንግድ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ በርካታ ነጋዴዎች ሃገሪቱ ባጋጠማት የውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳቢያ የውጭ ምንዛሪን ለማግኘት በአማካኝ እስከ ስድስት ወር ወረፋን እንደሚጠብቁ ሲገልፁ ቆይተዋል። በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ለፓርላማ የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርትን ረቡዕ ያቀረቡት የባንኩ ዋና ...

Read More »

በባህርዳር ከፍንዳታ ጋር በተየያዘ በጥርጣሬ በተያዙ ሰዎች ላይ የቴሌቪዥን ቀረጻ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ

ኢሳት (ሚያዚያ 26 ፥ 2009) ባለፈው ቅዳሜ በባህርዳር ከተከሰተው ፍንዳታ ጋር በተያያዘ በጥርጣሬ በተያዙ ሰዎች ላይ የቴሌቪዥን ቀረጻ በመካሄድ ላይ መሆኑን ምንጮች ለኢሳት ገልጹ። የገዢው ፓርቲ ምርት የሆነውን ባላገሩ ቢራ ለማስተዋወቅ በተጠራ የሙዚቃ ኮንሰርት አካባቢ በተከሰተ ፍንዳታ ፕሮግራሙ መቋረጡ ይታወሳል። በጥርጣሪ በተያዙት ግለሰቦች ላይ ማክሰኞ የተጀመረው ቀረጻ በአማራ ክልል ቴሌቪዥን አማካኝነት እየተፈጸመ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። ይህንን ሂደት በበላይነት የሚመሩት የማነ ...

Read More »

አሜሪካ ለአለም አቀፍ ድጋፍ በምትሰጠው የገንዘብ ድጎማ ላይ ያስተላለፈችው የበጀት ቅነሳ፣ ኢትዮጵያ ዋነኛ ተጎጂ ማድረጉ ተገለጸ

ኢሳት (ሚያዚያ 26 ፥ 2009) አሜሪካ በቅርቡ ለአለም አቀፍ ድጋፍ በምትሰጠው የገንዘብ ድጎማ ላይ ያስተላለፈችው የበጀት ቅነሳ፣ ኢትዮጵያ ዋነኛ ተጎጂ ማድረጉ ተገለጸ። ለኢትዮጵያና ኡጋንዳ የሚሰጠው ድጋፍ እንደሚቀንስም ተመልክቷል። ሃገሪቱ በተያዘው ሳምንት ባቀረበችው የ2017/2018 በጀት እቅድ በአለም አቀፍ የእርዳታ ላይ የ31 በመቶ አካባቢ ቅናሽ ማድረጓን ዘኢስት አፍሪካን የተሰኘ ጋዜጣ ዘግቧል። በዚሁ የአሜሪካ ዕርምጃ ኢትዮጵያና ዩጋንዳ ከአፍሪካ ዋነኛ ተጎጂ መሆናቸው ታውቋል። የኢትዮጵያ ...

Read More »

የሶማሊያው ፕሬዚደንት ሞሃመድ አብደላሂ በኢትዮጵያ ሲያደርጉ የነበሩትን ጉብኝት አቋርጠው ወደ ሃገራቸው ተመለሱ

ኢሳት (ሚያዚያ 26 ፥ 2009) በኢትዮጵያ ጉብኝትን በማድረግ ላይ የነበሩት የሶማሊያው ፕሬዚደንት ሞሃመድ አብደላሂ ረቡዕ በሞቃዲሾ ከተማ በአንድ ሚኒስትር ላይ የተፈጸመውን ግድያ ተከትሎ ጉብኝታቸውን አቋረጡ። ረቡዕ የሶስት ቀን ጉብኝትን ለማድረግ አዲስ አበባ ገብተው የነበሩት ፕሬዚደንቱ ከኢትዮጵያ እና ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመምከር እቅድ እንደነበራቸው ታውቋል። በአንድ ቀን ቆይታቸው ረቡዕ ምሽት በጠ/ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር የተወያዩ ሲሆን፣ ከሌሎች ...

Read More »

የአፋር ክልል የወረዳ ባለስልጣናት ለስብሰባ ወደ መቀሌ መሄዳቸው ተገለጸ

ኢሳት (ሚያዚያ 26 ፥ 2009) በአፋር ክልል የ33ቱም ወረዳ አመራሮች ለስልጠና መቀሌ ሲገቡ፣ የክልልና የወረዳ አመራሮች ደግሞ አዲስ አበባ መሄዳቸው ታወቀ። የወረዳ አመራሮች በአሳይታና በሰመራ መሰልጠን እየቻሉ ወደ መቀሌ መጓዛቸው በክልሉ ቅሬታ መፍጠሩን ምንጮች ገልጸዋል። ከአፋር 33ቱ ወረዳዎች ወደ መቀሌ የተጓዙ 600 ያህል አመራሮች ሲሆን፣ በቆይታቸው ወቅት የውሎ አበልም ሆነ፣ ሙሉ ለሙሉ የሆቴል ወጪያቸው የሚሸፈነው በአፋር ክልል መንግስት እንደሆነም ታውቋል። ...

Read More »

የተመድ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ የመንግስት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ያወጣውን ሪፖርት ውድቅ አደረጉት

ኢሳት (ሚያዚያ 26 ፥ 2009) በህወሃት አገዛዝ የተቋቋመው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በኢትዮጵያ ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ያወጣውን የምርመራ ሪፖርት በቅርቡ አዲስ አበባን የጎበኙት የተባባሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ውድቅ አደረጉት። ኮሚሽነሩ ዛይድ ራድ አልሁሴን በአዲስ አበባ በሰጡት መግለጫ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ብቻ ከ26 ሺ በላይ ሰዎች መታሰራቸውን እንዲሁም የተፈጸመው ግድያ በሃገሪቱ የህግ የበላይነት እንደሌለ ያሳያል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ...

Read More »

በቆላድባ አርሶአደሮች የግዳጅ ወታደራዊ ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ ነው

ሚያዝያ ፳፮ ( ሃያ ስድስት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከዚህ ቀደም በሰሜን ወሎ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች ሲካሄድ እንደነበረው አሁን ደግሞ በሰሜን ጎንደር አርሶአደሮች በግዴታ በእያካባቢያቸው ወታደራዊ ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ ነው። በቆላ ድባ ከተማ ከ150 በላይ አርሶአደሮች ተመልምለው ወታደራዊ ስልጠና እየወሰዱ ሲሆን፣ የከተማው ነዋሪ ቅሬታውን ሲገልጽ ተገደው እንደገቡ ተናግረዋል። አንዳንድ ሰልጣኞች ስልጠናውን ካልተካፈሉ የጦር መሳሪያቸውን እንደሚቀሙ ማስፈራሪያ የደረሳቸው ...

Read More »