.የኢሳት አማርኛ ዜና

የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሀገር መክዳትና በሽብር ወንጀል ተከሰሱ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 2/2010) የሰራዊቱን አባላት ለማስከዳትና ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጎን እንዲሰለፉ ሲቀሰቅሱ ነበር የተባሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የሀገር መክዳትና የሽብር ክስ ተመሰረተባቸው። ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ የታሰሩ ሰዎች ይፈታሉ የሚል መግለጫ በተሰጠ ማግስት ክስ የተመሰረተባቸው እነዚህ ወታደሮች 5 መሆናቸውም ታውቋል። ሕገመንግስታዊውን ስርአት ለመጠበቅ የተሰጣቸውን አደራ በመተው የኦነግን የሽብር ተግባር ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፣ሌሎች የሰራዊት አባላትንም ሲመለምሉ ነበር በሚል ክስ የተመሰረተባቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ...

Read More »

አቶ አባይ ወልዱ ከትግራይ ክልል ፕሬዝዳንትነት ተነሱ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 2/2010) በሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ሕወሃት/ግምገማ ከስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት የተባረሩት አቶ አባይ ወልዱ ከትግራይ ክልል ፕሬዝዳንትነት ቦታቸውም በይፋ ተነሱ። ሁለት የዞን አስተዳዳሪዎችም ከስልጣናቸው የተባረሩ ሲሆን የደህንነት ዋና ሃላፊው የአቶ ጌታቸው አሰፋ ወንድም ደግሞ የቢሮ ሃላፊ በመሆን ተሹመዋል። በቅርቡ የሕወሃት ሊቀመንበር ሆነው የተሾሙት ዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የትግራይ ክልልን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ መመረጣቸውም ይፋ ሆኗል። አቶ ደብረጺዮን ትግራይ ክልል በመመደባቸው ...

Read More »

በግብጽና ሱዳን መካከል የተጀመረው ውዝግብ እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 1/2010) ሱዳን ደሴቷን ለቱርክ መስጠቷን ተከትሎ በግብጽና ሱዳን መካከል የተጀመረው ውዝግብ መቀጠሉ ተሰማ። ግብጽ ወታደሮቿን ከሱዳን ጋር በሚያዋስነው የኤርትራ ድንበር ላይ ማስፈሯ የተገለጸ ሲሆን ሱዳንም ከኤርትራ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር ሙሉ በሙሉ ዘግታለች። ለግብጽና ሱዳን ውዝግብ መንስኤ የሆነው የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሪስፕ ጣይብ ኤርዶጋን ባለፈው ታህሳስ በሱዳን ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ በሁለቱ መንግስታት መካከል የተደረገው ስምምነት ነው። ሱዳን ነጻነቷን ካገኘችበት እንደ ...

Read More »

አንድ ጄኔራል ኢትዮጵያ ውስጥ ታሰሩ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 1/2010) አንድ የደቡብ ሱዳን ወታደራዊ ጄኔራል ኢትዮጵያ ውስጥ መታሰራቸው ተሰማ። ጄኔራሉ ለደቡብ ሱዳኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ታባን ዴንግ ጋይ የቅርብ ሰው ናቸው ሲል ራዲዮ ታማዙጅ ገልጿል። በኢትዮጵያ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር የዋሉት ብርጋዴር ጄኔራል ጋች ቶች ባለፈው ጥቅምት ድንበር አቋርጠው በጋምቤላ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ሲዘዋወሩ እንደነበር ዘገባው አመልክቷል። ጄኔራሉ በቁጥጥር ስር የዋሉበት ምክንያት ምንም አይነት ሕጋዊ ሰነድ ሳይኖራቸው ታርፓም በተባለ ...

Read More »

የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ስራ ጀመረ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 1/2010) የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ሕወሃት/ንብረት የሆነው ኤፈርት በ745 ሚሊየን ብር ያስገነባው የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ስራ ጀመረ። የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት በሳምንት 1 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኘው ይህ ፋብሪካ በቀን እስከ 5 ኪሎ ግራም ወርቅ ያመርታል። ኤፈርት ከዚህም በተጨማሪ በመላዋ ትግራይ የማዕድን ማልማት ስራዎችን ለማከናወን ከ8 የአሜሪካና የካናዳ ኩባንያዎች ጋር ስምምነት ላይ ደርሷል። በዚህ ስምምነት መሰረትም በትንሹ በአመት ከአንድ ...

Read More »

የእግር ኳስ ጨዋታ ግጭት አስከተለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 1/2010) በወልዲያ ከነማና በዋልዋሎ እግር ኳስ ቡድን መካከል በአዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደው የእግር ኳስ ጨዋታ ግጭት ማስከተሉ ታወቀ። ግጭቱ የተከሰተው ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ ሲሆን በፖሊስና በኳስ ደጋፊዎች መካከል ከተከሰተ መለስተኛ ግጭት ባለፈ የከፋ ጉዳት አለመድረሱም ታውቋል። የወልዲያ እግር ኳስ ቡድንና የትግራይ ክልሉ ዋልዋሎ የእግር ኳስ ቡድን የሚያደርጉት ጨዋታ ከሁለቱ ክልሎች ውጪ በአዲስ አበባ እንዲካሄድ የተወሰነው በክልሎቹ የሚካሄደው ውድድር ...

Read More »

በቄሮዎች ላይ ምርመራ ማካሄድ ህገወጥ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 1/2010) የኦሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ በቄሮዎች ላይ ምርመራ ማካሄድ ህገወጥ ነው አለ። ቢሮው ይህን ያስታወቀው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ባለፈው ሳምንት በቄሮዎች ላይ ምርመራ እያደረኩ ነው ማለቱን ተከትሎ ነው። የቢሮው የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ እንደተናገሩት የፌደራል ፖሊስ እያደረኩ ነው ስላለው ምርመራ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የሚያውቀው ነገር የለም። የሃላፊው መግለጫ ምርመራው ትኩረት ለማስቀየር የታለመ ነው የሚሉ የፖለቲካ ምሁራንን ...

Read More »

በጎረቤት ሀገር ሱዳን ከፍተኛ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2010) በዳቦ ዋጋ ላይ የተደረገ ጭማሪ በጎረቤት ሀገር ሱዳን ከፍተኛ ተቃውሞ ቀሰቀሰ። በአራት ከተሞች ህዝብ አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን የገለጸ ሲሆን በዚህም ተቃውሞ አንድ ሰው ሲገደል 6 ቆስለዋል። አመጹን አስነስተዋል በሚል ሶስት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ሲታሰሩ 6 ጋዜጦች ተዘግተዋል። በምዕራብ ዳርፉር ግዛት የተጀመረው ተቃውሞ ርዕሰ መዲናዋ ካርቱም መድረሱም ታውቋል። አልጀዚራ እንደዘገበው ትላንት እሁድ በምዕራብ ዳርፉር ግዛት መዲና ጌኒና የተጀመረው ...

Read More »

ዶክተር ፍቅሩ ማሩ የሞቱት ታካሚዎች ቁጥር 20 ደርሷል አሉ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2010) በከፍተኛ ጥበቃ ስር ሆኜ የልብ ሕሙማንን እንዳክም ጠይቄ ስላልተፈቀደልኝ የሞቱት ታካሚዎች ቁጥር 20 ደርሷል ሲሉ በእስር ላይ የሚገኙት ዶክተር ፍቅሩ ማሩ ለፍርድ ቤት ገለጹ። ከእስር ቤት ወደ ፍርድ ቤት በአቃቢ ሕግ ምስክር አለማቅረብ ምክንያት መመላለስ እንደመረራቸውም ታዋቂው የልብ ሃኪም ዶክተር ፍቅሩ ማሩ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በእስር ቤት እየደረሰባቸው ያለውን እንግልት ተናግረዋል። አቃቢ ሕግ ...

Read More »

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ሊያካሂድ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2010) የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ከጥር 12/2010 ጀምሮ ለ8 ቀናት በባህርዳር ከተማ እንደሚካሄድ የኢሳት ምንጮች ገለጹ። በስብሰባው ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ከአራት ጊዜ በላይ በጉባኤው ተመርጠው የሰሩ የብአዴን አባላት ይገኛሉ ተብሏል። ሕወሃትም ከጉባኤው በፊት ባልተለመደ ሁኔታ ከፍተኛ አመራሮች የሚገኙበት ድርጅታዊ ጉባኤ ከጥር 3/2010 ጀምሮ ለ8 ቀናት በመቀሌ እንደሚያካሂድ ታውቋል። ኢሳት ከምንጮች ያገኘው ሰነድ እንደሚያመለክተው የብአዴን ...

Read More »