ፕሬዚዳንት ኦባማ እስራኤልን እየጎበኙ ነው

መጋቢት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 

ኢሳት ዜና:-አሜሪካዊው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ እስራኤል ሲገቡ ፣ አገራቸው ለእስራኤል ጠንካራ ወዳጅ አገር መሆኑዋን ገልጸዋል። እስራኤል እንደ አሜሪካ ጠንካራ ወዳጅ የላትም ብለዋል ፕሬዚዳንቱ። ለቅድስቲቱ አገር ሰላም መምጣት እንዳለበትም ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንቱ ሀሙስ ወደ ዌስት ባንኩዋ ራማላህ ከተማ ተጉዘው ከፍልስጤም ባለስልጣናት ጋር ይነጋገራሉ። የፕሬዚዳንት ኦባማ ዋና የጉብኝት አላማ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ማደስ ነው ተብሎአል።

ፕሬዚዳንቱ ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በእስራኤል እና በአሜሪካ መካከል ያለው ግንኙነት ጥሩ አለመሆኑን ዘገባዎች ያመለክታሉ።

በኢራን የኒውክሊየር ጉዳይ ላይ በስልጣን ላይ ያለው የናታኒያሁ አስተዳደርና የኦባማ አስተዳደር የተለያዩ አቋሞች እንዳሉዋቸው ተንታኞች ይገልጻሉ።