ፎቶ ጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ ተሰደደ

 

መጋቢት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በተለያዩ ፎቶግራፎቹ ከፍተኛ እውቅና ያተረፈው ጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ አገሩን ጥሎ ለመሰደድ የተገደደው በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አገዛዝ አገሪቱን ሙሉ በሙሉ እያወደማት መሆኑን በመገንዘብ፣ የራሱን አስተዋጽኦ ለማድረግ ነው።

ጋዜጠኛ ቢንያም ከኢሳት ጋር ባደረገው ሰፊ ቃለምልልስ በስልጣን ላይ ያለው ሀይል ኢትዮጵያ በመኖርና ባለመኖር መካከል ከትቷታል።

በመንግስት የተበላሸ ፖሊሲ የተነሳ ኢትዮጵያ በፍጥነት ወደ ምደረ በዳነት እየተቀየረች መሆኑን በፎቶግራፍ በማስደገፍ ለኢሳት ገልጿል።

ፎቶ ጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ በሪፖርተር ጋዜጣ እና በአቢ ዊክሊ መጽሄት ሲሰራ ከቆየ በሁዋላ፣ ያራሱን ግላመር ፎቶ ስቱዲዮ በማቋቋም ፎቶ ኢግዢቢሺኖችን ማሳየቱን፣ በዚህም ስራው፣ የአገሪቱን መልካም ገጽታ አበላሽቷል በሚል በደህንነት ሀይሎች ሲዋከብ እንደነበር ገልጿል።

ከጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ ጋር የተደረገው ቃለምልልስ በቅርቡ ይቀርባል።

ሰሜንና ደቡብ ኮሪያ ተፋጠዋል