የፊታችን እሁድ የሚካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ቅስቀሳ  በአዲስ አበባ በጥሩ ሁኔታ ሲካሄድ በክልሎች እንቅፋት እየጋጠመው ነው

መጋቢት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በ9 የፖለቲካ ድርጅቶች ትብብር መጋቢት 20 በአዲስ አበባና በ15 የክልል ከተሞች የተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የትብብሩና የሰማያዊ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ለኢሳት ተናግረዋል።

ኢ/ር ይልቃል በግብርናና ገጠር ልማት ዙሪያ በሚደረገው የምርጫ ክርክርም እንዳይሰታፉ መከልከላቸውን ገልጸዋል።