የጣሊያን የድንበር ጠባቂዎች የ1 ሺ ሰዎችን ህይወት ማትረፋቸው ተገለጸ

ታህሳስ ፳፭( ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአብዛኛው የኤርትራ፣ ሶማሊያ፣ ዛምቢያ፣ ማሊና ፓኪስታን ዜጎችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች መርከብ ጉዳት ከመድረሱ በፊት የጣሊያን ጠባቂዎች ደርሰው እንዳዳኑዋት ቢቢሲ ዘግቧል።

ከሶስት ወራት በፊት ላምፓዱሳ እየተባለች በምትጠራዋ የጣሊያን ግዛት አቅራቢያ ከ400 በላይ ሰዎች መስጠማቸውን ተከትሎ የጣሊያን መንግስት ከፍተኛ ትችት ሲቀርብበት ቆይቷል። የአሁኑ እርምጃም ይህን ትችት ለማምለጥ የተወሰደ ይመስላል።

በአደጋው ከተረፉት መካከል 40 ህጻናትና 30 ሴቶች ይገኙበታል።