የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የመብራት እና ውሀ እጥረት አማረረን ይላሉ

ሚያዚያ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ መብራት ለተከታታይ ሶስት ቀናት ማግኘት ትልቅ ዜና እየሆነ ነው የሚለው ዘጋቢያችን፣ የመብራት መቋረጥን ተከትሎ በሚፈጠረው ችግር ባንኮች፣ አየር መንገዶችና ሌሎች ድርጅቶች ስራቸውን በተገቢው መንገድ ለመስራት እንዳልቻሉ ገልጿል።

ኢትዮጵያ ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ መጀመሩዋን የተናገረው መንግስት፣ መብራትን በፈረቃ ለማቅረብ መዘጋጀቱንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በመብራት እጦት ብቻ ሳይሆን በውሀ ችግርም እየተሰቃዩ ነው፡፡ አንዳንድ አካባቢዎች ካለፉት ሶስት ቀናት ጀምሮ ውሀ አላገኙም።