የአባይ ግድብ በተያዘለት እቅድ መሰረት ያለምንም ችግር እየተከናወነ ነው ሲሉ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሚኒስትር አለማየሁ ተገኑ ይህን የተናገሩት አንድ የግብጽ ጋዜጣ የአገሪቱን ከፍተኛ ባለስልጣን በመጥቀስ የዘገበውን ዜና ተከትሎ ነው። ጋዜጣው ፣ ኢትዮጵያ ለፖለቲካ ፍጆታ ለማዋል በማሰብ ግድቡ 30 በመቶ እንደተጠናቀቀ እያስወራች መሆኑዋንና ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት እንዳጋጠማት” መዘገቡ ይታወቃል።

የአባይ ግድብ ግንባታ የገንዘብም ሆነ የቴክኒክ ችግር አላጋጠመውም ያሉት ሚኒስትሩ፣ በተያዘለት የጊዜ ገደብም እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል። ይሁን እንጅ ይህ የተያዘለት የጊዜ ገደብ መቼ እንደሆነ አልገለጹም።

በግብጽ፣ ሱዳንና ኢትዮጵያ መካከል ሲደረግ የነበረው የሶስትዮሽ ውይይት መቋረጡን ተከትሎ፣ የግብጽ ወታደሮችና ፖለቲከኞች በቀጣይ ስለሚወስዱት እርምጃ እየመከሩ ነው።