የአባይ ግድብ ሰራተኞች ያስራ ማቆም አድማ በማድረግ ላይ ናቸው

የአባይ ግድብ ሰራተኞች ያስራ ማቆም አድማ በማድረግ ላይ ናቸው
( ኢሳት ዜና ነሐሴ 23 ቀን 2010 ዓ/ም ) ሰራተኞቹ አድማውን የጀመሩት ከደሞዝ እና ከአግልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ነው። ሰራተኞቹ የሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የበረሃ አበል መስተጓጎል፣ የሚከፈላቸው ክፍያ እና የሚሰሩት ስራ አለመመጣጠን ና የደህንነት ጅግሮች አድማውን እንዲያደርጉ እንዳስገደዳቸው ይገልጻሉ። ማኔጅመንቱ ሰራተኞችን ለማወያየት እቅድ መያዙን አስታውቋል።
ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ ለሜቴክ ተሰጥቶ የነበረውን የግንባታ ፕሮጀክት በመቀማት ለሌሎች ልምድ ላላቸው ኩባንያዎች ለመስጠት ፍላጎቱ እንዳላቸው አሳውቀዋል። የአባይ ግድብ ግንባታ ምን ያክል እንደተጠናቀቀ ባይታወቅም፣ ጠ/ሚኒስትሩ እንዳሉት ከ7 አመታት በሁዋላ አንድ ወይም ሁለት ተርባይኖች ተንቀሳቀስው ሃይል ማመንጨት አለመጀመራቸው የግንባታ ሂደቱ መጓተቱን የሚያሳይ ነው።