የታዋቂው የሬጌ አቀንቃኝ የቦብ ማርሌይ ሐውልት በአዲስ አበባ ሊቆም ነው።

ጥር ፲፪(አስራ ሁለት ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሐውልቱ  ስራ  አስተባባሪዎች መካከል  የጃኖ  ባንድ መስራች የሆነው አርቲስት አዲስ ገሰሰ  ለታዲያስ  አዲስ እንደገለጸው፤  የቦብ  ማርሌይ  ሐውልት  ከሶስት  ሳምንት  በሁዋላ  በገርጂ  ኢምፔሪያል ሆቴል ፊት ለፊት ይቆማል።

በምርጫ 97 ዋዜማ የቦብ ማርለይ 60ኛ አመት በመስቀል አደባባይ  ሲከበር፤ በወቅቱ  የመዲናዋ  ከንቲባ  የነበሩት አቶ አርከበ  እቁባይ  በበአሉ የተገኙትን የቦብ ማርለይ ቤተሰቦችን ሐውልቱ ይቆምበታል ወደተባለው ስፍራ በመውሰድ፦<በሲህ ቦታ የቦብ ማርለይ ሐውልት  እንዲቆም ወስነናል”በማለት ቃል መግባታቸው ይታወሳል።

አቶ አርከበ   ከአስር ዓመት በፊት ቃል ቢገቡም፤ በተለያዩ  ምክንያቶች እስካሁን  ሐውልቱ ሳይቆም  መቆየቱን  የገለጸው አርቲስት አዲስ፤ ከሶስት ሳምንት በሁዋላ  በተባለው ቦታ በይፋ እንድሚቆም አሳውቋል።