የምርጫ 97 የሰኔ 1 ሰማዕታት ታስበው ዋሉ

ሰኔ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በምርጫ 97 ወቅት “የተጭበረበረው የወላጆቻችች ድምጽ ይመለስ” በማለት ወደ አደባባይ ወጥተው  በግፍ የተጨፈጨፉት የምርጫ 97 ሰምአታት 8ኛ አመት በተለያዩ ዝግጅቶች ታስቦ ውሎአል።

በሟቹ ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ ትእዛዝ ከ100 በላይ ኢትዮጵያውያን ሰኔ አንድ ቀን 1997 ዓም በአጋዚ ወታደሮች መጨፍጨፋቸው ይታወሳል። በተፈጥሮ ሞት ከተለዩት ከአቶ መለስ ዜናዊ በስተቀር ጭፍጨፋውን በመምራት የተባበሩት ሌሎች ባለስልጣኖች ዛሬም ድረስ ለፍርድ አልቀረቡም።

አንድነት ፓርቲ፣  መኢአድ  እንዲሁም የሰማእታት ቤተሰቦች አመቱን በልዩ ክብር የሚዘክሩት ሲሆን፣ በዛሬው እለትም ቀኑ ተከብሮ ውሎአል።

በምርጫ 97 ወቅት የተሰውት ወጣቶች ለዲሞክራሲያዊ ስርአት በሚታገሉ ሀይሎች ዘንድ ” የዲሞክራሲ አርበኞች” እየተባሉ ይጠራሉ።