ኬንያ በኢቦላ በሽታ የመጠቃት እድሏ ከፍተኛ ነው ተባለ

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጊኒ ፣ ሴራሊዮንና ላይቤሪያ የታየው የኢቦላ ወረርሽኝ ወደ ሌሎች የአፍሪካ አገራት እንዳይዛመት ከፍተኛ

ስጋት በደቀነበት በዚህ ወቅት፣ ከምስራቅ አፍሪካ ኬንያ በበሽታው ከሚጠቁ ቀዳሚ አገራት ተርታ ተሰልፋለች።ኬንያ የብዙ የምእራብ አፍሪካ አገራት

የትራንስፖርት ማእከል በመሆኗ በበሽታው የመጠቃት እድላን ከፍ እንዳደረገው የተባበሩት መንግስታት የጤና ድርጅት አስታውቋል። ጀርመን ዜጓቿ

ከላይበሪያ፣ ጊኒና ሴራሊዮን እንዲወጡ ስታዝ፣ጋናደግሞየትምህርት ቤት የመክፈቻ ጊዜን አራዝማለች። የምእራብ መንግስታት ለሙከራ የተዘጋጁ

መድሃኒቶችን እየለገሱ መሆኑን እየገለጹ ነው።