ኢ/ር ይልቃል ከአገር አንዳይወጡ የተከለከሉበትን ምክንያት የሚነግራቸው  ማጣታቸው ተዘገበ

መጋቢት ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሰማያዊ ፓርቲ ሊ/መንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ወደ አሜሪካ ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ በደህንነት ሰዎች እንዲሰረዝ ከተደረገ በሁዋላ፣ እስካሁን ድረስ ምክንያቱን የሚነግራቸው አካል መጥፋቱን ሊ/መንበሩ

ለነገረ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የኢሜግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ መስሪያ ቤት ‹‹ፓስፖርቱ እኛ ጋር አልደረሰም፡፡ ቆይተው ደውለው ይጠይቁ››  ብለው ስልክ እንደሰጧቸው የገለጹት ኢ/ር ይልቃል፣ ይህም ሆን ተብሎ ጉዞውን ለማጓተት የተደረገ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ይህን ሁሉ የሚያደርጉት አገር የማስተዳደር

ብቃት ስለሌላቸው፣  የፖለቲከኛን እንቅስቃሴ በማጓተትና በማገድ የተፈጠረባቸውን ስጋት የሚቀርፉ ስለሚመስላቸው ነው፡፡  ከአቅመ ቢስነታቸው የመነጨ ነው›› ሲሉ ለጋዜጣው ተናግረዋል፡፡

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ሰማያዊ ፓርቲ በውጭ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ያለው ተቀባይነት ገዢውን ፓርቲ እንዳስፈራውም አክለዋል።