አቶ ስብሐት ነጋ ስለ አቶ መለስ ዜናዊ በ10 ቀናት ውስጥ መመለስ መናገራቸው ስህተት እንደነበረ ለኢሳት ገለጡ

ነሀሴ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-አቶ መለስ ዜናዊ በ10 ቀናት ውስጥ ወደ ስራ ገበታቸው እንደሚመለሱ ከሶስት ሳምንት በፊት ያስታወቁት አቶ ስብሐት ነጋ አባባላቸው ስህተት መሆኑን ለኢሳት ገለጡ።

አቶ በረከት ስምኦን ከአዲሱ አመት በፊት አቶ መለስ ወደ ስራ ገበታቸው እንደሚመለሱ የሰጡትን መግለጫ በተመለከተ ይህንን የማረጋገጥም ሆነ የማስተባበል መረጃ እንደሌላቸው አመልክተዋል።

አንጋፋው የህወሀት ታጋይ አቶ ስብሀት ነጋ ለስርአቱ ቅርበት ያላቸው ጋዜጦች አቶ መለስ ወደ ሀገር ቤት ስለመመለሰሳቸ በጻፉት ጥያቄ አንስተዋል። ከሰኔ 11/2004ዓም ጀምሮ ላለፈት 57 ቀናት አቶ መለስ ዜናዊን አለማግኘታቸውን አቶ ስብሀት ለኢሳት በሰጡት ቃለምልልስ አመልክተዋል።

የሀገሪቱ ጦር ሀይል አዛዥነቱን ስልጣን የያዘው ማነው ፣ አቶ መለስ በህይወት ካሉ ድምጻቸውን ለምን አያሰሙም? የሚሉት ጥያቄዎች ቀርበውላቸው መልስ ሰጥተዋል።

____________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide