አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥር 16 በመቶ ጨመረ

ነሀሴ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ግብርና ሚኒስቴር እና የውጭ ለጋሾች ትናንት በጋራ ያቀረቡት ሰነድ እንደሚያሳየው ከሀምሌ እስከ ታህሳስ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር ከ3 ሚሊዮን 200 ሺ ወደ 3 ሚሊዮን 700 ሺ ከፍ ብሎአል። ለእነዚህ ተረጅዎች ከ189 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ3 ቢሊዮን 4 መቶ ሚሊዮን በላይ ብር እንደሚያስፈልግ ታውቛል።

41 በመቶ የሚሆኑት ተረጅዎች በሶማሊ፣ 27 በመቶ በኦሮሚያ፣ 10 በመቶ በትግራይ፣ 8 በመቶ በአማራና በደቡብ፣ እንዲሁም 4 በመቶ በአፋር ክልል ይገኛሉ።

በአጠቃላይ 193 ሺ 866 ሜትሪክ ቶን ምግብ እንደሚያስፈልግ በሰነዱ ተመልክቷል።

ይህ አሀዝ በአለም ባንክና በሌሎች የምእራብ አገራት ምግብ ለስራ በሚል መርሀ ግብር የታቀፉትን 8 ሚሊዮን ተረጅዎች አይጨምርም። የእነዚህ ተረጅዎች ቁጥር በተረጅዎች ቁጥር ውስጥ ሲገባ ከኢትዮጵያ ህዝብ ከ16 በመቶ ያላነሰው በውጭ በሚሰጥ ምጽዋት የሚኖር ነው።

የግብርና ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ሶስት አመታት በምግብ ራሳችንን እንችላለን ብለው ከትናንት በስቲያ መናገራቸው ይታወሳል። ይሁን እንጅ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በምግብ ራሱዋን ለመቻል በርካታ አመታት ትጠብቃለች።

ኢትዮጵያን ላለፉት 21 አመታት የመሩት አቶ መለስ ዜናዊ ከ15 አመታት በፊት በምግብ ራሳችንን እንደምንችል መናገራቸው ይታወሳል።

____________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide