ተፈናቃይ አርሶአደሮች የደረሰባቸውን ጉዳት በመዘርዝር ለመንግስት ባለስልጣናት አቀረቡ

መጋቢት ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በትናንትናው እለት ከቤንሻንጉል ጉሙዝ እና ከአማራ ክልል የተውጣጡ ከፍተኛ ባለስልጣናት ፍኖተሰላም ከተማ ላይ ሰፍረው የሚገኙትን ተፈናቃዮች ያነጋገሩ ሲሆን፣ ተፈናቃዮችም ልዩ ሀይል እየተባለc በሚጠራው ታታቂ ቡድን የደረሰባቸውን ግፍ ያለምንም ፍርሀት ማቅረባቸውን በስብሰባው ላይ የተሳተፉ አንድ ተፈናቃይ ገልጠዋል።

በስብሰባው ላይ ከአማራ ክልል መገናኛ ብዙሀን የተውጣ  ጡ ጋዜጠኞች ቢገኙም፣ ስብሰባውን እንዳይቀርጹ መደረጉን አንድ በስፍራው አለው የኢሳት ወኪል ገልጿል። አካባቢው በፌደራል በፖሊስ የሚጠበቅ በመሆኑን ፎቶግራፍ ማንሳትም ሆነ ሰዎችን ማነጋገር እንዳልተቻለ መኪላችን ገልጿል።

ከ 3 ሺ በላይ ተፈናቃዮች በፍኖተ-ሰላም ከተማ እንደሚገኙ መዘገባችን ይታወሳል። በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናት እስካሁን ድረስ ይፋ መግለቻ አልሰጡም።