ተስፋ የቆረጡ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አሰሙ

ህዳር ፲፰(አስ ስምንት )ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-በርካታ ተስፋ የቆረጡ ኢትዮጵያውያን መዲናህ ከተባለው መጠለያቸው  ግንብ እየዘለሉ  ወደ ታይባን ዩኒቨርስቲ ካምፓስ እንደገቡ የአገሪቱ ፖሊስ አስታውቋል።

ብርጋዴር ፋህድ ቢን አሚር አል ጋናም እንደገለጹት 15 ኢትዮጵያውያን ወደ ዩኒቨርስቲው ግቢ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ሀይሎች ኢትዮጵያውያኑን በመያዝ ወደ ማጎሪያ ካምፓቸው ልከዋቸዋል።

ኢትዮጵያውያኑ በሰዎች፣  በመኪኖች ወይም ህንጻዎች ላይ ጉዳት እንዳላደረሱ የሳውዲ ዩኒቨርስቲ ቃል አቀባይ ገልጸዋል፡

ኢትዮጵያውያኑ ወደ አገራቸው ለመመለስ ቪዛ የማግኘቱ ሂደት ስለዘገየባቸው ተቃውሞ ለማድረግ መገደዳቸው ታውቋል።
ታይባህ ዩኒቨርስቲ መዘጋቱም ታውቋል።

በኢትዮጵያውያን ላይ ስለደረሰው ጉዳት ለማወቅ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። በሳውድ አረቢያ ውስጥ አሁንም በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ለመመለስ በመጠባባቅ ላይ ይገኛሉ።