በጋዜጣ አዙዋሪዎች ላይ እርምጃ መወሰድ መጀመሩ ታወቀ

 

ግንቦት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሰማያዊ ፓርቲ ልሳን የሆነው ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው  ሃሙስ ምሽትላይ  በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ጋዜጣ አዙዋሪዎች በገዥው ፓርቲ የደህንነት ኃይሎች ታግተው አምሽተዋል፡፡የደህንነት ኃይሎች ‹‹ለማዞር የተደራጃችሁበትንና ፈቃድ የተሰጣችሁበትን ወረቀት አምጡ›› በማለት ወደ ጣቢያ ሊወስዱዋቸው እንደ ነበርና አዙዋዎቹም ‹‹መደራጀት አይጠበቅብንም ፣ጣቢያም አንሄድም›› ብለው የደህንነቶቹን ትዕዛዝ መቃወማቸውን ጋዜጣው ዘግቧል፡፡ መንግስትን የሚተቹ ጋዜጦችና መጽሄቶች እንዲያዞሩ እንደማይፈልግና እሱ የሚፈልገውን እያደራጀ መሆኑን አዙሪያዎቹ ለጋዜጣው  ገልጸዋል፡፡  ‹‹መንግስት በእኛ ብቻ ሳይሆን ጋዜጣ በምናስነብብባቸው ካፌዎች ላይም ጫና ተጀምሯል፡፡ካፌዎቹ ለአንድ ሰው ከአንድ ጋዜጣ በላይ እንዳንሰጥ ናአንዳንዶቹም ጭራሹን እንዳናስነብብና እንዳንሸጥ እየከለከሉንነው፡፡›› በማለት አዙዋሪዎቹመናገራቸውን ጋዜጣው ዘግቧል።

ኢሳት ጥር 28 ቀን 2006 ዓም “መንግስትአንዳንድብቅበማለትላይያሉነጻጋዜጦችንለመቅጨትእየሰራነውተባለ” በሚል ርእስ ባወጣው ዘገባ “የመንግስትኮምኒኬሽንጉዳዮችጽ/ቤትየጋዜጦችናየመጽሔቶችንስርጭትአስተካክላለሁበሚልያዘጋጀውንመጠይቅካለፈውሳምንትጀምሮለሚዲያዎችናለአከፋፋዮችበማስሞላትላይሲሆንዋናአላማውምአንዳንድብቅበማለትላይያሉትንነጻጋዜጦችንለመቅጨትያለመመሆኑን ጠቅሷል።

መንግስትእስከዛሬበስርጭትስራላይየተሰማሩዋናአከፋፋዮችከግብር፣ታክስናከመሳሰሉትሕጋዊሁኔታዎችጋርተያይዞክስበመመስረት  ስራውንምለአነስተኛናጥቃቅንተቋማትለመስጠትሃሳብመኖሩን ዘግቦ ነበር፡፡