በአፋር ክልል በተነሳ ግጭት ከ10 ያላነሱ ሰዎች ተገደሉ

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የአካባቢው ተወላጆች ለኢሳት እንደተናገሩት ጥቃቱን የፈጸሙት በሶማሊ ክልል በሚደገፉ የኢሳ የልዩ ሀይል አባላት ናቸው። ትናንት ከጧቱ 12 ሰአት ላይ በመደበኛ ሁኔታ የታጠቁ ልዩ ሀይሎች 10 ሰዎችን መግደላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ  እንደሚሉት መንግስት ጥቃቱ ሲፈጸም ሊታደጋቸው አልቻለም (2፡45-03፡08)። ጥቃቱን የፈጸሙት ሀይሎች በሶማሊ ክልል እና በጂቡቲ መንግስት የሚደገፉ ልዩ የኢሳ  ሀይል ታጣቂዎች መሆናቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች አሁንም በከፍተኛ ፍርሀት ውስጥ መውደቃቸውን እና ፌደራል ፖሊስ አባላት ሊከላከሉላቸው አለመቻላቸውን  ይናገራሉ::

በጥቃቱ 5 ሰዎች ቆስለዋል፣ አንደኛው በከባድ ሁኔታ በመቁሰሉ ራሱን እንደማያውቅ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የአፋር ሂውማን ራይትስ ድርጅት በክልሉ እየተፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በማውገዝ መግለጫ አውጥቷል። የድርጅቱ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ጋአስ አህመድ  በተለያዩ ዞኖች የሚፈጸሙት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ከስኳር ልማትና ከማእድን ጋር የተያያዙ መሆኑን ጠቅሰው፣ በትናንትናው እለት ብቻ 21 ሰዎች መገደላቸውን ገልጠዋል ።

አቶ ገአስ የኢትዮጵያ መንግስት ታጣቂዎች ግድያዎች ሲፈጸሙ ቆመው መመልከታቸው አገዛዙ ከድርጊቱ ጀርባ እጁ እንዳለበት የሚያመለክት ነው::

አቶ ገአስ እንደሚሉት ከጨው ምርት ጋር በተያያዘ በተነሳ ውዝግብም ሁለት ወረዳዎች ተፋጠው ይገኛሉ።

በአፋር ጉዳይ ስለተገደሉት ሰዎች የክልሉም ሆነ የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት የሰጡት አስተያየት የለም።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide