በስዊዘርላንድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያውያን የአድዋን በአል አከበሩ

መጋቢት ፳( ሃያ ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ቅዳሜ ማርች 27፣ 2016 በተደረገው የአድዋ በአል ዝግጅት ላይ ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያኖችና የውጭ አገር ዜጎች ተገኝተው በአሉን አክብረዋል፡፡ የበአል ዝግጀቱ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ውሂብ የሽጥላ ፣ አድዋ የኢትዮጵያች ብቻ ሳይሆን የመላው ጥቁሮች ድል በመሆኑ ወጣቶችና ታዳጊዎች ታሪካቸውን እንዲያውቁ ማድረግ ሃላፊነታችን ነው ብለዋል፡፡
በጄኔቭ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት ረዳት ፕ/ር ኤስቴል ሶዬ የኢትዮጵያ ነገስታትና የውጭ ግንኙነታቸው ምን እንደሚመስል ያዘጋጁትን ጥናት በተለያዩ ፎቶዎች በማስደገፍ አቅርበዋል፡፡
የእለቱ ተጋበዠ እንግዳ የሆኑት ዶ/ር አረጋዊ በርሄ የአድዋ ድል ሲፈነጥቅ በሚል ርእስ ወረቀት አቅርበዋል፡፡ ወ/ሮ ብርሃኔ በበኩላቸው ሴቶችና አድዋን በተመለከተ ንግግር አድርገዋል፡፡ የተለያዩ ስነ‹ሁፎችና ንግግሮች በተሳታፊዎች ቀርበዋል፡፡ በመጨረሻም በድምዊያን ቤተልሄም ዳኛቸውና ሲሳይ የተለያዩ ዘመናዊና ባህላዊ ሙዚቃዎችን በማቅረብ ዝግጅቱ ተጠናቁዋል፡፡