ሰማያዊ ፓርቲ በተሳካ ሁኔታ ባዘጋጀው የተቃውሞ ሰልፍ ህዝቡ ደስታውን እየገለጸ ነው

ግንቦት ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ሰማያዊ ፓርቲ ትናንት በተሳካ ሁኔታ ያካሄደውን ሰልፍ በተመለከተ የተለያዩ ወገኖች ለኢሳት እየደወሉ ደስታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው። ፓርቲው ተቃውሞውን ከማዘጋጀት ጀምሮ አጠር እና ምጥን ያለ ዝግጅት በማቅረቡ ደስታቸውን የገለጸት አንድ አስተያየት ሰጪ፣ ተቃውሞው ብልጭታ እንድናይ አድርጎናል ብሎአል

አንድ ሌላ ሴት ደግሞ በትናንትናው ሰልፍ “ትንሽ ትንሽ” ዲሞክራሲ እየመጣ ይመስለኛል ብለዋል

ሌላ አስተያየት ሰጪ ደግሞ ተቃውሞው ከሚጠበቀው በላይ መሳካቱን ገልጸው ቀኑ ፍርሀት የተሰበረበት ነበር ብለዋል