ሞጆዎች በውሀ ተጠማን አሉ

ሰኔ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-አንዳንድ ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት በከተማዋ ውሀ  ከጠፋ  20 ቀናት አልፈዋል። በአብዛኛው የከተማ ክፍል ውሀ አለመኖሩን ነው ነዋሪዎች የሚናገሩት

በጉዳዩ ዙሪያ የሞጆ ከተማ ባለስልጣናትን አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

በአዲስ አበባም እንዲሁ በተለያዩ ቦታዎች  የውሀ እጥረት መከሰቱን መዘገባችን ይታወቃል።