መቀሌ የትግራይ ሰማአታትን አክብራ ዋለች

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :- በደርግ ዘመን በአየር ድብደባ የሞቱ የሀውዜን ነዋሪዎች እና ታጋዮች ለ5ኛ ጊዜ በመቀሌ ከተማ ታስበው ውለዋል።

የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡት በሀውዜን በደረሰው ጭፍጨፋ ከ2500 በላይ ሰዎች ተገድለዋል፤ በትጥቅ ትግሉም ወቅት 40 ሺ በላይ የህወሀት  ታጋዮች ተገድለዋል።

የክልሉ ፕሬዚዳንት አባይ ወልዱ ወጣቱ ትውልድ የሰማእታቱን አላማ ከግብ ለማድረስ እንዲረባረብ አሳሰበዋል።

በሀውዜን ለደረሰው ጭፍጨፋ የደርግ ባለስልጣናት ብቻ ሳይሆኑ ጭፍጫውን ያቀነባበሩት የህወሀት ሰዎችም ተጠያቂ መሆን አለባቸው በማለት የቀድሞው የህወሀት ታጋይ አቶ ገብረመድህን አርአያ መናገራቸው ይታወሳል።