ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ እንደገለጹት በሶሪያ የበሽር አላሳድን መንግስት ለመገልበጥ የተቃውሞ ትግል ከተጀመረበት ካለፉት 3 አመታት ጀምሮ ከ100 ሺ ህዝብ በላይ ተገድላል። የተባበሩት መንግስታት ድርጀት ባለፈው ወር ካወጣው አሀዝ ጋር ሲነጻጸር የማቾች ቁጥር በ7 ሺ ከፍ ብሎአል። ባንኪሙን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒሰትር ጆን ኬሪ ጋር በመሆን ነው መግለጫውን የሰጡት። ሁለቱም ወገኖች ለሶሪያ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሁለተኛ ዙር መዋጮ የመንግስት ሰራተኞች ፈቃደኛ አልሆኑም ተባለ
ሐምሌ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው አመት የወር ደሞዛችን በአመት ከፍለናል አሁን ግን ዳግመኛ ለመከፈል አቅሙ ስሌለለን እና እየተባባሰ የመጣውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም ስለማንችል፣ ከእንግዲህ ወዲህ ገንዘብ ልንከፈል የምንችለው ባገኘንበት ጊዜ ብቻ ነው ” በማለት በአማራ ክልል የሚገኙ የመምህራን ማህበራት አስታውቀዋል፡፡ መንግስት ከሐምሌ ወር ጀምሮ ከሰራተኛው ለመቁረጥ አቅዶት የነበረ ቢሆንም ፣ በክልል ቢሮዎች ብቻ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የመንግስት ...
Read More »የፓርላማው ውይይት መታፈኑን ያጋለጠው የኢቲቪ ጋዜጠኛ ከሥራ ተባረረ
ሐምሌ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት “የዴሞክራሲ ተቋማት ሚናና የአስፈፃሚ ተቋማት ኃላፊነት” በሚል ርዕስ ጥቅምት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ያደረገውን ውይይት በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በኩል ተቆራርጦና ተዛብቶ እንዲተላለፍ ተደርጓል በሚል አንድ ዜና መዘገቡ ይታወሳል። ዜናው በሰንደቅ ጋዜጣ የህዳር 5 ቀን 2005 ዓ.ም ዕትም “ኢቲቪ የከፍተኛ ባለሥልጣናትን ውይይት በማፈን ተወቀሰ” በሚል ርዕስ ከቀረበ በኋላ፤ በዚህ ...
Read More »የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እንዲከፈት ቅዱስ ሲኖዶሱ ቢወስንም ተግባራዊ አልሆነም ተባለ
ሐምሌ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ተማሪዎቹ ያነሷቸውን ጥያቄዎች የተመለከቱት ፓትሪያሪኩ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በኮሌጁ ይሰጥ የነበረው የትምህርት እና የምግብ አገልግሎት እንዲቀጥል እና ተመራቂ ተማሪዎችም በወቅቱ እንዲመረቁ የወሰኑ ቢሆንም ተማሪዎቹ ግን እስከትናንት ድረስ ትምህርት አለመጀመራቸውን ተማሪዎቹን አነጋግሮ ሰንደቅ ዘግቧል። የተማሪዎች መማክርት ሰብሳቢው ዲያቆን ታምርአየሁ አጥናፌ ለጋዜጣው እንደገለጸው፣ ሐሙስ እለት ውሳኔውን ሰምተው ቢሄዱም ጊቢው ውስጥ ግን የተለወጠ ነገር አልነበረም፣ ...
Read More »በአማራ ክልል የሚደርሰው የመኪና አደጋ ጨምሯል።
ሐምሌ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በክልሉ አራት አመት በማይሞላ ጊዜ ውስጥ 8 ሺ 2 መቶ 46 የመኪና አደጋ የተከሰተ ሲሆን ፣ 5 ሺ 101 ዜጎች እጃቸውን እና እግራቸውን አጥተው ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ በኢትዩጵያ በየደቂቃው ከሞት ጋር የሚጋፈጡ የመኪና አደጋ ችግር የሰው ልጅ ራስ ምታት ሁኗል፡፡ የመኪና አደጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከመቀነስ ይልቅ ሲጨምር እንደሚታይ የገለፁት ኑዋሪዎች የመንግስት ...
Read More »መንግስት ሕዝበ ሙስሊሙን ለማውገዝ የሠላም ኮንፈረንስ ጠራ
ሐምሌ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላትን በማንቀሳቀስ አገር አቀፍ የሠላም ኮንፈረሰንስ ለማካሄድ መዘጋጀቱን ይፋ አደረገ፡፡ መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ እንደማይገባ ሕገመንግስቱ ቢደነግግም የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በሕገመንግስት አስተምህሮ ስም የሃይማኖት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጭምር በማቋቋም የመብት ጥያቄ በማቅረባቸው ምክንያት የታሰሩና የሽብርተኝነት ክስ የቀረበባቸውን የሕዝበ ሙስሊም ማህበረሰብ አባላትና ደጋፊዎቻቸውን እንቅስቃሴ ለማፈን አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል ሲሉ አንድ ...
Read More »የፕሮቴስታንት ሀይማኖት ተከታዮች እየተሳደድን ነው አሉ
ሐምሌ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሰሜን ወሎ ዞን ከወልድያ ከተማ በ140 ኪሜ ርቅት ላይ በትምገኘዋ መቀት ወረዳ የሚገኙ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ከፍተኛ እንግልት እደረሰባቸውና አካባቢውንም ለቀው እንዲወጡ ግፊት እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን በደረሰን መረጃ 10 የሚሆኑ የሀይማኖቱ ተከታዮች አካባቢውን ለቀው የወጡ ሲሆን፣ አንድ ተመስገን የተባለ ወጣት ለተባባሪ ዘጋቢያችን እንደገለጸው አማኞቹ ድንጋይ ይወረወርባቸዋል፣ ቤታቸውም በድንጋይ ይደበደባል። ተመስገን ሀምሌ 1 ...
Read More »በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ከተሰጠው ብድር ውስጥ 1 ቢሊዮን ብር አልተመለሰም
ሐምሌ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢህአዴግ ልሳን የሆነው ፋና እንደዘገበው ከ2003 ዓመተ ምህረት ጀምሮ በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ለተሰማሩ ማህበራት 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ብድር ቢሰጥም ከ1 ቢሊየን ብር በላይ የሚሆነው አልተመለሰም ። ብድርን በማስመለስ በኩል የቅንጅት እጦት ፣ አስቀድሞ የመስሪያ ቤቶችን ያለማዘጋጀትና የገበያ ትስስሮሽን በበቂ ሁኔታ አለመፍጠር መሰረታዊ ጅግሮች መሆናቸው ተጠቅሷል። ገንዘብ ተበድረው ከሃገር የሚጠፉ ፣ በቂ ...
Read More »በደቡብ ወሎ ዞን በሚገኘው ኩታበር ወረዳ አንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. በደሴ ያካሄደውን ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በመቃወም ህዝቡ ሰላማዊ እንዲወጣ ኢህአዴግ እያስገደደ መሆኑን ፍኖተ ነፃነት ዘገበ ፡፡
ሐምሌ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሰልፉ ረቡዕ ሐምሌ 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ጠዋት ላይ እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡ በወረዳው ቀበሌ 05፣06 እና 07 ሰፊ የማስፈራሪያና የቅስቀሳ ስራ እየተካሄደ መሆኑንም ጋዜጣው ዘግቧል፡፡ ጋዜጣው የኢህአዴግ ካድሬዎች ገበሬውን በግድ ከአቅሙ በላይ የዘር ማዳበሪያ ውሰድ እያሉ ከፍተኛ ገንዘብ ከማስከፈላቸው በተጨማሪ ለአማራ ልማት ማኀበር፣ለአባይ፣ ለመሬት ግብር እየተባለ የሚጠየቀው መዋጮ በመብዛቱ ነዋሪዎቹ ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ሲናገሩ ...
Read More »በስዊዘርላንድ የተካሄደው በአውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የስፖርት በአል በተሰካ ሁኔታ ተጠናቀቀ
ሐምሌ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኒዮን የስዊዘርላንድ ከተማ የተካሄደው 11ኛው የአውሮፓ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል ቅዳሜ ጁላይ 20 በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል። ከተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት፣ ከሰሜን አሜሪካ፣ ከኢትዮጵያ እንዲሁም ከተለያዩ አህጉራት የመጡ በርካታ ኢትዮጵያውንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ለበዓሉ ድምቀት አስተዋጽዖ አድርገዋል። ይህ በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን ፌስቲቫል ላለፉት 11 ዓመታት በተከታታይ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፣ በአህጉሪቱ የሚገኙና ከሌሎች አህጉራትም ጭምር በመሰባሰብ በርካታ ኢትዮጵያውያን ...
Read More »