ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፒያሳ ከሚገኘው ኑር መስጊድ አንስቶ ዙሪያውን ባሉ መንገዶች ላይ ቆሞ የረመዳንን ጁመዓ ስግደት ሲሰግድ የዋለው ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ፣ ከአንድ አመት በላይ ሲያሰማው ነበረውን ድምጻችን ይሰማ የሚለውን ተቃውሞ በከፍተኛ ድምጽ በማሰማት የፒያሳን አየር ተቆጣጥሮት ውሎአል። ድምጻችን ይሰማ፣ የተነጠቅነውን መስጂዶቻችን ለህዝቡ ይመለሱ፣ የተባረሩ ኢማሞች ይመለሱ፣ አሸባሪ አይደለንም፣ ኢማሞቻችን ይፈቱ፣ ጥያቄው ይመለስ፣ ህገ መንግስቱ ይከበር፣ መጅሊሱ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
በአርሲ አንድ አድማ በታኝ ፖሊስ አዛዥ በጩቤ ተወግቶ ተገደለ
ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሻለቃ ማእረግ ያለው ፖሊስ አዛዥ በተለያዩ የሰውነት ክፍሎቹ ላይ በጩቤ ተወግቶ መገደሉን የደረሰን ዜና ያመለክታል። ግድያውን ተከትሎ ፖሊስ በትናንትናው እለት እና ዛሬ ከፍተኛ ፍተሻ ሲያካሂድ ውሎአል። የገዳዮቹ ማንነት እስካሁን አልታወቀም። በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከወትሮው በተለየ ቁጥር በየቦታው ፍተሻ ሲያኪዱ የታዩት የፌደራል ፖሊሶች፣ ምናልባትም ግድያውን ከሙስሊሞች ጥያቄ ጋር ሊያያይዙት እንደሚችሉ ፍንጮች መታየት መጀመራቸውን ጉዳዩን ...
Read More »ከ 27 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ይጠይቃል የተባለ የቴሌኮሙኒኬሽን ማስፋፊያ ሥራ ለቻይና ኩባንያ ተሰጠ።
ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከስልክ ኔትወርክ ጥራት ጋር በተያያዘ በየጊዜው የሚነሳውን ቅሬታ ይፈታል የተባለ እና 1ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከ 27 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የጠየቀ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ ”ሁዋዌ”ለተሰኘው የቻይና ኩባንያ ትናንት ተሰጠ። የፕሮጀክቱን ውል ስምምነት ትናንት ማምሻውን ኢትዮ ቴሌኮም እና የቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ ጋር ተፈራርመዋል። ፊርማውን የኢትዮ ቴሌኮም ተቀዳሚ ስራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም አድማሴ ...
Read More »በስፔን የደረሰውን አሰቃቂ የባቡር አደጋ ተከትሎ የባቡሩ ሾፌር በቁጥጥር ስር መዋሉን ቢቢሲ ዘገበ።
ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአገሪቱ ሰሜናዊ ምዕራብ ከተማ በሆነችው በሳንቲያጎ ደ-ኮምፖስቴላ ረቡዕ እለት በደረሰው የባቡር አደጋ 78 ሰዎች ሲሞቱ 130 ሰዎች ተጎድተዋል። ከ130ዎቹ ቁስለኞች መካከል 35 ቀላል እርዳታ ተደርጎላቸው ከሆስፒታል የወጡ ሲሆን ከበድ ያለ ጉዳት የደረሰባቸው 95 ሰዎች በሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ ይገኛሉ። የባቡሩን ሾፌር ለአደጋው ተጠያቂ ያደረገው የስፔን ፖሊስ ፤አደጋው በሚደርስበት ጊዜ ባቡሩ ከተፈቀደው ፍጥነት ከእጥፍ በላይ ...
Read More »በግብጽ የፕሬዚዳንት ሙርሲ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎችን አደረጉ
ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፕሬዚዳንት ሙሀመድ ሙርሲ ደጋፊዎች በቁጥጥር ስር የዋሉት ፕሬዚዳንቱ ወደ ስልጣን እንዲመለሱ ሲጠይቁ ፣ የእርሳቸው ተቃዋሚዎች ደግሞ ፕሬዚዳንቱን ከስልጣን ላወረደው የመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ለመስጠት በታህሪር አደባባይ ተገኝተዋል። ለፕሬዚዳንቱ ከስልጣን መወገድ ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት ጄኔራል አብደል ፋታህ ኤል ሲሲ ሰሞኑን ህዝቡ ለወሰዱት እርምጃ ድጋፋቸውን እንዲሰጣቸው ተማጽነው ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ ፕሬዚዳንት ሙሀመድ ሙርሲ ከፍልስጤሙ ...
Read More »ከ40 በላይ የቁጫ ወረዳ ሽማግሌዎች ጉዳያቸውን ለፌደራል መንግስቱ አቀረቡ
ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሀምሌ ወር መግቢያ በደቡብ ክልል በጋሞጎፋ ዞን በቁጫ ወረዳ በሰላም በር ከተማ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የታሰሩትን ከ60 በላይ የከተማዋ ታዋቂ ሰዎችን ለማስፈታት እና ላቀረቡትም ጥያቄ መልስ እንዲሰጣቸው ለመጠየቅ በትናንትናው እለት 40 አገር ሽማግሌዎች ወደ አዲስ አበባ በመሄድ ጥያቄአቸውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቅርበዋል። ምክር ቤቱም ጥያቄውን የማየት ስልጣን ያለው የክልሉ መንግስት በመሆኑ አጥጋቢ መልስ ...
Read More »በኢትዮጵያ የሚታየው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ተባብሷል
ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ኃይል በፈረቃ የማዳረስ ተግባር በሚስጢር ማከናወኑን አጠናክሮ መቀጠሉን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ በተለይ በአዲስአበባ ከሰኔ ወር 2005 አጋማሽ ጀምሮ በተከታታይ የኤሌክትሪክ ኃይል በመቋረጥ ላይ የሚገኝ ሲሆን በአንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች የኃይል መቋረጡ በተከታታይ እስከሶስት ቀናት የሚወስድ ጭምር መሆኑ ነዋሪውን ሕዝብ ግራ የሚያጋባ ሆኗል፡፡ የኃይል መቆራረጡ እንደባንክ፣ አየር መንገድ ያሉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ...
Read More »በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የአጭር ጊዜ ቪዛ አሳጣጥ አሰራሩ ላይ ለውጥ እንደሚያደርግ አስታወቀ
ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስአበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2005 ጀምሮ ወደአሜሪካን ለሚጓዙ ሁሉ የቪዛ ሒደትን የሚያቃልል አዲስ አሰራር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡ ኤምባሲው ትላንት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንደጠቀሰው የአሜሪካን ኤምባሲ የቪዛ ሒደት ክፍያን ከፍለው ቀጠሮ ያስያዙ አመልካቾች ከሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2005 ዓ.ም በፊት ቀጠሮ እንዲይዙ በጥብቅ አሳስቧል፡ ቀጠሮአቸውም ከሐምሌ 24 ቀን 2005 በፊት ...
Read More »የዱከም ድልድይ ግንባታ ውል እንዲቋረጥ ተወሰነ
ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ወጪና ገቢ ንግድ ዕቃዎች የሚስተናገዱበት ዋና ጎዳና ላይ የዱከም ድልድይን ለመገንባት የተረከበው አክሽን ኢንጂነሪንግ ኩባንያ ሥራውን በውሉ መሠረት ባለማከናወኑ የኮንትራት ውሉ እንዲቋረጥ መወሰኑ ተገለጸ፡፡ ሪፖርተር ምንጮቹን በመጥቀስ እንደዘገበው “ጎጊቻ” በሚባለው ወንዝ ላይ የተጀመረው የድልድይ ግንባታ በውሉ መሠረት እየተከናወነ ባለመሆኑና የግንባታው መጓተት እያስከተለ ያለውን ችግር ከግምት በማስገባት፣ ከኮንትራክተሩ ጋር የተገባው ውል እንዲቋረጥና ሥራው ...
Read More »የአዲስ አበባ መስተዳደር ከ18 ሄክታር በላይ መሬት ማስመለሱን ገለጸ
ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መስተዳድሩ በሊዝ ለማልማት መሬት ወስደው በተቀመጠላቸው ጊዜ ውስጥ ካላለሙ 284 አልሚዎች መሆኑን የኢህአዴግ ልሳን ሆነው ፋና ዘግቧል። ባለፉት 5አመታት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት ከህገወጥ ወራሪዎች ተነጥቆ ወደ መሬት ባንክ መግባቱንም መስተዳድሩ አስታውቋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ 155 ሄክታር መሬት በመልሶ ማልማት የለማ ሲሆን፥ ከ2 ሺህ 900 ሄክታር በላይ ...
Read More »