.የኢሳት አማርኛ ዜና

በደብረዘይት በሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ተፈናቀሉ

ሐምሌ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የከተማው ባለስልጣናት ትናንት በቀበሌ 01 በድንገት በጀመሩት የቤት ማፍረስ እንቅስቃሴ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ቤት አልባ ሆነዋል። ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኦሮምያ ፖሊስ በአካባቢው ሰፍሮ እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ከመቆጣጠር አልፎ ፣ ህጻናትንና ወጣቶችን እየደበደቡ አፍሰው ማሰራቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል። ብዙዎች በእለቱ በጣለው ዝናብ የቤት እቃዎቻቸው ተበላሽቶባቸዋል። ” ቤታችን ለምን ይፈርሳል ብለዉ የጠየቁ ዜጎች መድረክ ...

Read More »

በአርባምንጭ አንድ ወጣት ሰቆቃ ተፈጸመበት

ሐምሌ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወጣት ባንተወሰን አበበ ያልምንም ተጨባጭ መረጃ ሃምሌ 6፣ 2007 ዓም ከታሰረ በሁዋላ ከፍተኛ የሆነ ድብደባ እንደተፈጸመበት ለኢሳት ተናግሯል። ባንተወሰን ከተያዘ ከሁለት ቀናት በሁዋላ ፍርድ ቤት ቢቀርብም፣ ዳኛው በዋስ እንዲለቀቅ ማዘዛቸውን ይሁን እንጅ ፣ ፖሊስ አልፈታም በማለት ፣ ሃምሌ 17 ከምሽቱ 12፣ 40 ላይ ከእስር ቤት አውጥተው ሰቆቃ ( ቶርቸር) እንደፈጸሙበት ገልጿል። ...

Read More »

የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ ተባብሶ ቀጥሎአል

ሐምሌ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዚህ አመት በአገሪቱ የታየው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እየከፋ በመሄዱ፣ በጥቁር ገበያ እና በህገወጥ መንገድ የሚደረገው የዶላር ዝውውር መድራቱን ዘጋቢአችን ገልጿል። ከውጭ ንግድ ጋር በተያያዘ ስራቸውን የሚሰሩ ነጋዴዎች ዶላር እንደልባቸው ለማግኘት ባለመቻላቸው፣ ዶላርን ከጥቁር ገበያና ከባንኮች በልዩ ሁኔታና በውድ ዋጋ ለመግዛት እየተገደዱ ነው። የተወሰነ መጠን ዶላር ለማግኘት ለባንክ ባለስልጣናት ኮሚሽን መክፈል ...

Read More »

በሽዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አይሁዶች ወደ እስራኤል ለመግባት እየተጠባበቁ ነው

ሐምሌ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቁጥራቸው ከስምንት ሽህ በላይ የሚሆኑ ቤተ እስራኤላዊያን እስራኤል ውስጥ ከሚገኙት ቤተሰቦቻቸው ጋር ለመገናኘት እየተጠባበቁ ሲሆን አብዛሃኞቹ ከአስራ አምስት ዓመታት በላይ ከወላጆቻቸው የተለያዩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የቀድሞ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ”እነዚህ አይሁዳዊያን ናቸው በየዕለቱም ይፀልያሉ” ሲሉ ፣ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስቴሩ በበኩላቸው ”ውሳኔ በአፍጣኝ ያልተሰጣቸው በዘረኝነት ተፅዕኖ ምክንያት ነው”ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።የአገሪቱ የስደተኞች ...

Read More »

80 በመቶ የኢህአዴግ መሪዎች ችግር ፈችዎች አይደሉም ተባሉ

ሐምሌ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀጣይ አምስት አመታት የስልጣን ድልድል ቅድመ አቋም ግምገማ ለመጀመሪያ ጊዜ ለውይይት በቀረበበት ወቅት እንደተገለጸው፣ 80 በመቶ የኢህአዴግ ሚኒስትሮች ችግር የምፍታት አቅም የላቸውም። ለግምገማ በቀረቡት የተለያዩ መስፈርቶች ብቃት አላቸው የተባሉት አቶ በረከት ስምኦን ሲሆኑ፣ ጠ/ሚኒስትሩን ጨምሮ አብዛኞቹ ሚኒስትሮች ችግር ፈችዎች አይደሉም ተብለዋል። ቅድመ አቋም ግምገማውን ያካሂዱት ከአራቱም የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች የተውጣጡ ነባር ...

Read More »

በባህር ዳር ከተማ የተከሰተው የነዳጅ እጥረት ህዝቡን እያማረረ ነው

ሐምሌ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በነዳጅ እጥረት ምክንያት የየዕለቱን ስራ ለመስራት የባጃጅ ኮንትራት በመያዝ ለአላስፈላጊ ወጭ መዳረጋቸውን የሚገልጹት የከተማ ነዋሪዎች ጠዋትእና ማታ በሚኖረው ረዣዢም ሰልፍ ምክንያት ስራ ቦታቸው በሰዓት ለመውጣትና ለመግባት መቸገራቸውን ለዘጋቢያችን ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በነዳጁ መጥፋት ለረዢም ሰዓታት ስራ መፍታታቸው በኑሯቸው ላይ ችግር እየፈጠረ መሆኑን የሚናገሩት በከተማዋ የሚገኙ የባጃጅ አሽከርካሪዎች የነዳጅ ዋጋ መቀነሱን ...

Read More »

የጊኒ ዎርም በሽታ በኢትዮጵያ እየተስፋፋ መሆኑ ተገለጸ

ሐምሌ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ከምድረ ገጽ ጠፍቶ የነበረው ጊኒ ዎርም በሽታ እንዳዲስ ማንሰራራት መጀመሩ በአዲስ አበባው ሀገር አቀፍ የጤና ጉባኤ ላይ ተገልጿል፡፡ ዶ/ር ዳዲ ጅማ ፣ በኢትዮጵያ በሽታው በደቡብ ክልል እና በጋምቤላ በፍጥነት በሰዎች ላይ መታየት መጀመሩን የጤና ባለሙያዎችን መረጃ ዋቢ በማድረግ ወቅታዊውን ሪፖርት ከጥናታቸው ጋር አዛምደው አቅርበዋል። በጥቅምት 2011 የመከረው ...

Read More »

የአዲስ አበባ መንገዶች በጎርፍ እየተጥለቀለቁ ነው

ሐምሌ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባ ጎዳናዎች የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦዎች የሌላቸው እስኪመስል ድረስ እግረኞች ብቻ ሳይሆኑ አሽከርካሪዎችም ጭምር መንገድ ለማቋረጥ ሲሳናቸው ተስተውሏል። በርካታ የአዲስ አበባ መንገዶች ከዓመት እስከ ዓመት ተመሳሳይ ችግሮች ቢስተዋልባቸውም መንገድ ትራንስፓርት የፍሳሽ ማስወገጃዎችን በመስራትና የተበላሹትን ጠግኖ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ አልቻለም። የከተማው ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ቢያሰሙም ችግራቸውን ሰምቶ መፍትሔ የሚሰጣቸው አካል ግን እስከ ...

Read More »

ፕሬዚዳንት ኦባማ በሰላም አስከባሪ ስም ተሸፍኖ የቀረበውን ተቃዋሚዎችን በሽብርተኝነት የሚፈርጀውን ጥያቄ ሳይቀበሉት ቀሩ

ሐምሌ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፕ/ት ባራክ ኦባማ ከአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ባደረጉት ውይይት፣ በውጭ አገር በተለይም በአሜሪካ የተቀመጠ ተቃዋሚ ድርጅት በሽብረተኝነት እንዲፈረጅ የቀረበውን ጥያቄ ሳይቀበሉት ቀርተዋል። አቶ ሃይለማርያም ” ሽብርተኝነትን በመዋጋት እንዲሁም ሰራዊታችንን በጸጥታ አስከባሪነት ስም ለመላክ የማንችልበት ደረጃ ላይ እየደረሰን ነው” የሚል ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን፣ ለዚህም የሰጡት ምክንያት “በኤርትራ በኩል የሚነሱ ታጣቂ ሃይሎች የፈጠሩትን ...

Read More »

በሙስና የሚዘጉ የፍርድ ቤት መዝገቦች በዝተዋል ተባለ

ሐምሌ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ12ኛው የፍትህ ሚኒስቴርና የክልል ፍትህ ቢሮዎች የጋራ መድረክ ላይ እንደተነገረው በበጀት አመቱ የተቋረጡ መዝገቦች በሙሉ ኦዲት ተደርገው ሲጣሩ፣ በአጠቃላይ የፍርድ ቤት መዝገቦች የተዘጉት በክራይ ሰብሳቢነት፣በዝምድናና በተያያዙ የገንዘብ ጉዳዮች መሆኑን የስብሰባው ተሳታፊዎች ተናግረዋል። የደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊ በክልላቸው በስፋት በሚታየው ህገወጥ የሰወች ዝውውር ላይ በሰጡት አስተያየት ፣ በርካታ ወጣቶች ወደ ደቡብ ...

Read More »