ሐምሌ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአገሪቱ ደቡባዊ ምዕራብ ጀዛን ከተማ ውስጥ በአንድ ሳውድ አረቢያዊ ዜጋ ላይ ዝርፊያና ግድያ ፈፅመዋል ተብለው የተከሰሱት ሁለቱ ኢትዮጵያዊያን ፣ አረጋዊ አልዶ ኃ/ማሪያም እና ሃዲሽ ዘላለም ናቸው። ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አንገታቸውን ተቀልተው የሞት ፍርድ ተፈፅሞባቸዋል ሲል የሳዑዲ አረቢያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስቴሩን ጠቅሶ ታይምስ ላይቭ ዘግቧል። በሌላ ወንጀል የተከሰሰው የአገሪቱ ዜጋ የሆነው ሙሻሻ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ከ15 ዓመታት በኃላ የሥጋ ደዌ ሕመም አገረሸ
ሐምሌ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዓለም አቀፍ ደረጃ መጥፋቱ የሚነገርለት የሥጋ ደዌ ሕመም በአዲስ መልክ በኢትዮጽያ ማገርሸቱ አስደንጋጭ መሆኑን የኢትዮጽያ የቆዳና የአባላዘር በሽታዎች ሕክምና ማህበር በሂልተን ሆቴል ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ ላይ ይፋ አደረገ፡፡ በሽታው በዓለም አቀፍ ደረጃ መጥፋቱ የተረጋገጠው ከ15 ዓመታት በፊት መሆኑ የተነገረ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት ግን በኢትዮጵያ በዓመት ከ4ሺ በላይ አዳዲስ ሕሙማን መታየት ...
Read More »ስድስት ከፍተኛ ዲፕሎማቶች የህወሃት/ኢህአዴግ ስርአትን መክዳታቸው ታወቀ
ኢሳት ዜና (ሃምሌ 28 2007 አ ም ) በተለያዩ የአገልግሎት ክፍሎች በተለያዩ የሀላፊነት ደረጃዎች ላይ ሲያገለግሉ የነበሩ 6 ዲፕሎማቶች ስርአቱን በመክዳት እንደወጡ መቅረታቸው ታወቀ ። የአገልግሎት ጊዜያቸውን በማጠናቀቅና በተለያዩ ምክንያቶች ለኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እስከ ሀምሌ 1 2007 ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቦላቸው ለጥሪው ምላሽ በመንፈግ ስርአቱን የከዱ ዲፕሎማቶች ከአሜሪካ አፍሪካና ህንድ መሆኑን የውጪ ጉዳይ ምንጮች ገልጸዋል። በአሜሪካ ደቡብ አፍሪካ ጋና ...
Read More »ድምጻችን ይሰማ ትግሉን እንደሚቀጥልበት አስታወቀ
ሐምሌ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ አቡበክር አህመድን ጨምሮ በ18 የድምጻችን ይሰማ የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላት ላይ የተላለፈውን የፍርድ ውሳኔ “ድራማ ነው” በማለት ያጣጣለው ድምጻችን ይሰማ ፣የተሰጠው ፖለቲካዊ ፍርድ “ትግሉን የበለጠ እንድንቀጥልበት ያደርገናል” ሲል ገልጿል። የፍርዱን ኢ-ፍትሃዊነት የመንግስት ባለስልጣናትና ድራማውን የተወኑት አቃቢ ህግጋት እና ዳኞች ሳይቀር ያውቁታል የሚለው ድምጻችን ይሰማ፣ ውሳኔው ” የበለጠ እንታገል ዘንድ የሚያነሳሳ ...
Read More »በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ድርቅ መግባቱ ታወቀ
ሐምሌ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጋቢዎቻችን እንዳሉት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ከዝናብ እጥረት ጋር ተያይዞ ድርቅ ተከስቷል።በሰሜን ሸዋ፣በዋግ ህምራና በወሎ በርካታ ቦታዎች ዝናብ ባለመዝነቡ ድርቅ ገብቷል፡፡ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ጉዳዩን በዝግ ስብሰባዎች ቢወያዩበትም ፣ መረጃው ወደ አደባባይ እንዳይወጣ ጥረት እያደረጉ ነው። በዋግ ህምራ አካባቢ ለሶስተኛ ጊዜ እርሻ እየተገለበጠ በመታረስ ላይ መሆኑን ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘ ...
Read More »በኢግዚቢትነት የሚያዙ እቃዎች በፖሊሶች ይዘረፋሉ ሲሉ ሚኒስትሩ ተናገሩ
ሐምሌ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ጌታቸው አምባዩ በቅርቡ በተካሄደው የፌደራል እና ክልል የፍትህ ምክክር መድረክ ላይ ፣ አቃቢ ህግ ክስ ሲመሰርት ከክሱ መግለጫ ጋር ስለ ተያዙ ኤግዚቢቶች ስለማይጠቅስ ፣ ንብረቶቹ በፖሊስ ጣቢያዎች ለረዢም ጊዜ ያለጥንቃቄ በመቆየታቸው በሚደርስባቸው የአያያዝ ጉድለት እንደሚበላሹ እና በፖሊስ አባላትም ያለአግባብ እንደሚዘረፉ ገልጸዋል፡፡ ሚኒስትሩ ይህን ይበሉ እንጅ ያቀረቡት የመፍትሄ ሃሳብ ...
Read More »በድምጻችን ይሰማ የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላት ላይ ከባድ ቅጣት ተላለፈ
ሐምሌ ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአቶ አቡበክር አህመድ የክስ መዝገብ ስር የሚገኙ የድምጻችን ይሰማ የመፍትሄ አፈላላጊ አባላት ከ22 እስከ 7 አመታት በሚደርስ እስር እንዲቀጡ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት ውሳኔ አስተላልፏል። ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ፍርዱን ፍርድ ነው ብለን ለመቀበል አስቸጋሪ ነው ብለውታል። ፍርድ ቤቱ አቶ አቡበክር አህመድ፣ አህመዲን ጀበል፣ ያሲን ኑሩ እና ከሚል ሸምሱ ...
Read More »የአዲስ አበባ የኢህአዴግ ግምገማ አባላቱን ከሁለት ከፈለ
ሐምሌ ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በየደረጃው በሚገኙ በኢህአዴግ ድርጅት ኃላፊዎች የተመራውና በተያዘው በጀት ዓመት ከተማዋን ይመራሉ ተብለው የሚሾሙ የድርጅት ካድሬዎችን የሚለይበት የከተማና የክ/ከተማ ከፍተኛ የግምገማ መድረክ አጋማሹን ካድሬ አስደስቶ አጋማሹን ደግሞ አሳዝኖና አበሳጭቶ ተጠናቋል፡፡ በሃምሌ ወር የመጀመሪያ ሳምንት ላይ የተጀመረው ይህ ግምገማ በልዩ ትኩረት አጀንዳ ተቀርፆለት በተቀመጠለት መርሃ ግብር መሰረት በአጠቃላይ 20 ...
Read More »ለሳሙኤል አወቀ መታሰቢያ ደም ተለገሰ
ሐምሌ ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ደብረማርቆስ ከተማ ውስጥ ለተገደለው ወጣት ሳሙኤል አወቀ መታሰቢያ ሀምሌ 26 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት ደም ተለግሷል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎችም ሳሙኤልን ለማስታወስ የተገኙ ግለሰቦች ደም ሰጥተዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ በዛሬው ቀን ደም መስጠት ያስፈለገው ሳሙኤልን ለማስታወስ መሆኑን ገልጾ ...
Read More »በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ከ 40 በላይ የአየር ሀይል ባለሙያዎች መክዳታቸው ታወቀ
ኢሳት ዜና (ሃምሌ 24, 2007) በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ከ 40 በላይ የአየር ሀይል ባለሙያዎችና ሰራተኞች በስልጣን ላይ ያለውን ሰርአት በመክዳት ወደተለያዩ ቦታዎች መሰወራቸው ታወቀ ። የኢሳት የአየር ሀይል ምንጮች እንደገለጹት የደብረዘይት አየር ሀይል ጠቅላይ መምሪያ በወታደራዊ የስራ መደብ የሚያገለግሉትን ጨምሮ 14 ቴክኒሺያኖችና ለጊዜው በቁጥር ያልተገለጹ አብራሪዎች ባለፈው አንድ ወር በስራ ገበታቸው አልተገኙም። በዋና ማዘዢያ ጣቢያና በዘመቻ መምሪያ የአየር ሀይል ...
Read More »