ኀዳር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ፖሊስ እና የደህንነት ሃይሎች ከባህርዳር ከተማ በስተደቡብ በ35 ኪሜትር ርቀት ላይ በምትገኘዋ መራዊ ከተማ በመገኘት የከተማዋን ወጣቶችንና ነዋሪዎችን ከሌሊቱ አስራ አንድ ሰአት ላይ እየደበደቡ አፍነው ወስደዋቸዋል። የሰማያዊ ፓርቲ አባላት አቶ መኳንንት ጸጋዬን እና አቶ እያዩ መጣን ጨምሮ አእምሮ መጣ፣ ሽባባው የኔአለምና አብርሃ ተሰራ የተባሉ ነዋሪዎች ታስረዋል።የፌደራል ፖሊስ አባላት በአካባቢው የሚያደርጉትን አሰሳ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
እነ አቶ ሀብታሙ አያሌው አቃቤ ህግ የጠየቀው ይግባኝ ተቀባይነት አገኘ
ኀዳር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ ተበይኖላቸው የነበሩት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ላይ አቃቤ ህግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት የጠየቀው ይግባኝ ያስቀርባል በመባሉ ክሱ እንደገና ሊታይ መሆኑን ነገረ ኢትዮጵአ ዘግቧል። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ‹‹ይግባኙ ያስቀርባል ” በማለት መወሰኑን ተከትሎ ይግባኝ የተጠየቀባቸው ተከሳሾች ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ...
Read More »የብአዴን ንብረት የሆነው አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ፍትሃዊ ያልሆነ ከፍተኛ ወለድ በማስከፈል ህብረተሰቡን እየበዘበዘ ነው ተባለ
ኀዳር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአማራ ክልል በስፋት በመሰማራት የአነስተኛ ነዋሪውን ህይወት ለመቀየር ትልቅ መፍትሔ አለው በማለት የገዢው መንግስት በስፋት እየሰራበት ያለው የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም፣ ከሌሎች የባንክ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በተለየ ከፍተኛ ወለድ በማስከፈል ህብረተሰቡን እየበዘበዘ መሆኑን ደንበኞች በተለይ ለኢሳት ተናግረዋል፡፡ የብድር ተቋሙ በየአካባቢው በሚከፍታቸው ቅርንጫፎች ሌሎችን የብድርና ቁጠባ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን የተለያየ ምክንያቶችን በመፍጠር ...
Read More »ሱዳናዊያን በኢትዮጵያ ታጣቂዎች ጥቃት እየደረሰብን ነው አሉ
ኀዳር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አቅራቢያ የጸጥታው ሁኔታ እየተባባሰ መምጣቱንና በሱዳናዊያን በግፍ ለተገደሉት ኢትዮያዊያን አፋጣኝ አጸፋዊ ምላሽ የሰጡት የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ታጣቂዎች ሃምሳ መንደሮችን በቁጥጥራቸው ስር ማድረጋቸውንና ሃያ ለሚሆኑ ያገቷቸውን ሱዳናዊንን 360ሺህ የሱዳን ዲናር ማለትም 59 ሽህ ዶላር አስከፍለው መልቀቃቸው ተዘግቧል። የገዳሪፍ የግህ አውጭ ካውንስል ሊቀመንበር የሆኑት ሞሃመድ ኤል ማርዲ፣ ሰፊ መሬት የተቆጣጠሩት ...
Read More »ለመንግስት ባለስልጣናት ለእያንዳንዳቸው 25 ሚሊዮን ብር ወጪ ሆኖ የሚሰራላቸው ቤት የህዝብ ህዝቡን እያነጋገረ ነው
ኀዳር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለስድስት ከፍተኛ ጡረተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለእያንዳንዳቸው በ25 ሚሊየን ብር ወጪ በስጦታ የሚለገሳቸው የመኖሪያ ቤት እየተገነባ መሆኑ ሰሞኑን በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ከሆነ በሁዋላ በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል፡፡ በተለይ በረሃብ ምክንያት ከ 15 ሚሊየን ያላነሱ ወገኖችን ችግር ላይ በወደቁበት፣ በከተሞች አካባቢ ከፍተኛ ኑሮ ውድነትና የስራ አጥነት በነገሰበት፣ የመንግስት ሠራተኛው ሳይተርፈው ...
Read More »የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ተማሪዎችን በብሄር ብሄረሰቦች መብት ዙሪያ እንዲያወያዩ ታዘዙ
ኀዳር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢሳት በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደር ጉዳዮች ሃላፊ በሆኑት በዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ኪዳኔ ተጽፎ ለእያንዳንዱ ዩኒቨርስቲ የተሰራጨው የኢሜል መልእክት ከኢሳት የትምህርት ሚኒስቴር ምንጮች የደረሰው ሲሆን፣ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች በሞላ ተማሪዎችን ህዳር 29 ለሚከበረው 10ኛው የብሄር ብሄረሰቦች በአል እንዲያወያዩ ታዘዋል። በቀረበው የውይይት ሰነድ በተራ ቁጥር 7 ላይ ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚጠበቀው ግዴታ ምን እንደሆነ በዝርዝር ቀርቧል። ...
Read More »ረዳት ፓይለት ኃይለመድህን አበራ የስነልቦና ችግር አለበት በሚል ክሱን ማንሳቱን የስዊዘርላንድ ፍርድ ቤት አስታወቀ
ኀዳር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ረዳት አብራሪ የነበረውና በድርጅቱ ውስጥ ያለው ዘረኝነትና አድሎዋዊ አሰራር ስራዬን በነጻነት ለመስራት አላስቻለኝም በሚል ምክንያት ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሆነውን ከአዲስ አበባ ተነስቶ በካርቱም በኩል አቋርጦ ወደ ጣሊያን ይበር የነበረን ቦይንግ 767-300 አውሮፕላን በመጥለፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ካሰረፈ በሁዋላ ጉዳዩን ሲከታተለው የነበረው ፍርድ ቤት ክሱ እንዲነሳ ወስኗል። ረዳት ፓይለት ኃይለመድህን ...
Read More »የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ኦራል መኪና ተገልብጦ በትንሹ 20 ወታደሮች ህይወታቸው ሲያልፍ በርካቶችም ቆስለዋል
ኀዳር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዛሬ ህዳር 2፣ 2008 ዓም ከጎንደር ወደ መተማ ሲጓዙ ከነበሩ ኦራል መኪኖች መካከል አንደኛው ግንድ መጣያ ቀበሌ ልዩ ስሙ ባለእግዚብሄር ቦታ ላይ ሲደርስ ባጋጠመው የቴክኒክ መበላሸት የተነሳ በመገልበጡ በሸራ ተሸፍነው ሲጓዝ ከነበሩት ወታደሮች መካካል 20 የሚሆኑት ወዲያውኑ ሲሞቱ፣ በርካታ ቁጥር ያላቸው ወታደሮች ቆስለው ወደ ጎንደር ሆስታል ተወስደዋል። ቦታው ላይ የነበሩ የአይን ...
Read More »በኮንሶ ውጥረቱ ተባብሶ ብዙዎች በጅምላ እየታሰሩ ነው
ኀዳር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በደቡብ ክልል ሰገን ዞን ኮንሶ ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች በዞን ደረጃ ራሳቸውን ለማስተዳደር እንዲፈቅድላቸው ጥያቄ በማቅረባቸው ብቻ የብሔረሰቡን አባላት ማሳደድ፣ ማሰር፣ መደብደብ ዘመቻው የቀጠለ ሲሆን፣በአካባቢው ያለው ውጥረት ተባብሷል፡፡ የደቡብ ክልል መንግስት የኮንሶን ጥያቄ በአግባቡ ከመመለስ ይልቅ ጥያቄውን በኃይል ወደማፈን በመሸጋገሩ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ ከጉዳዩ ጋር እጃቸው አለበት የተባሉ በርካታ ሰዎች ከያሉበት ...
Read More »በወልድያ ታዋቂ ባለሃብቶች ታሰሩ
ኀዳር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በከተማው ከሚገኙና በአብዛኛው የገዢው ፓርቲ ዋነኛ ደጋፊ ባለሃብቶች ተብለው ከሚታወቁት መካከል 14 ቱ በአራጣ ማበደር ወንጀል ተከሰው ከሶስት ቀናት በፊት ታስረዋል። ከተያዙት ባለሃብቶች መካከል አቶ ስማቸው፣ አቶ ዘገየ መላኩ፣ ዶ/ር በቀለ፣ ሞላ ጌታሁን፣ አውዱ፣ ኪዳኔ ካህሳይ፣ አበበ ደመቀ፣ አቶ እስራ፣ ፖለስ ጌታው አበሬ፣ እንዲሁም አቶ ካሳሁን ይገኙበታል። ባለሀብቶቹ የብአዴን ባንክ ከሆነው ...
Read More »