.የኢሳት አማርኛ ዜና

የአዳማ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በአጋዚ ወታደሮች ግድያ፣ ድብደባና ወከባ ደረሰባቸው

ኢሳት (ታህሳስ 26 ፥ 2008) በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለውን የመሬት ዘረፋና የጅምላ ጭፍጨፋን  በመቃወም ላይ በነበሩ በአዳማ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ተቃውሞውን ለማስቆም በተሰማሩ የጸጥታ ሃይላት መካከል ግጭት እንደተፈጠረ የአይን እማኞች ከስፍራው አስታወቁ። ሰኞ ጠዋት የተጀመረው ይህ ተቃውሞ፣ ተማሪዎቹ በአዳማ ዩንቨርስቲ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በኦሮሚያ ክልልና በሌላው የኢትዮጵያ ክልሎች ላይ እየደረሰ ያለው ጭፍጨፋና፣ ወከባና፣  እንግልትን እንዲቆም ሲጠይቁ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። አመጹን ለማስቆም ...

Read More »

ኢትዮጵያ ኪስማዩን ለማስለቀቅ ጦሯን ወደሶማሊያ አሰማራች

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፥ 2008) የሶማልያ የወደብ ከተማ የሆንችዉን ኪስማዩ ከሶማሊያዉ ታጣቂ ሀይል አል-ሸባብ ለማስለቀቅ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ወታደሮችንና ታንኮችን ወደ ስፍራዉ ማሰማራቷ ተገለጠ። የታጣቂ ሀይሉ ጠንካራ ይዞታ እንደሆነች የሚነገርላትን ኪስማዩ ለማስለቀቅም በአካባቢዉ በማንኛዉም ሰአት ከባድ ዉጊያ ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት መኖሩን የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታዉቀዋል። እሑድ ወደ ወደባማ ከተማዋ የገቡት በመቶዎች የሚቆጠሩት የኢትዮጵያ ወታደሮች በታጣቂ ሀይሉ ቁጥጥር ስር የምትገኘዉን ከተማ ነጻ ለማዉጣት ...

Read More »

በሶማሌ ክልል በሊበን ዞን በሚገኙ ወረዳዎች የዉሃ-ወለድ ተላላፊ ወረርሽኝ ተከሰተ

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፥ 2008) በሶማሊያ ክልል እየተባባሰ የመጣዉን የድርቅ አደጋ ተከትሎ በሊበን ዞን በሚገኙ ወረዳዎች የዉሃ ወለድ ተላላፊ በሽታዎች ወረርሽኝ መከሰቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰኞ አስታወቀ። በሽታዉን ለመቆጣጠርም የተለያዩ የጤና ተቋማት ርብርብን እያደረጉ እንደሚገኙና ወረርሽኙ ወደ ተጎራባች ዞኖች ለመዛመት ይችላል የሚል ስጋት መኖሩን ድርጅቱ ገለጿል። ባለፈዉ ወር ተመሳሳይ ወረርሽኝ በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ አካባቢ ተቀስቅሶ የነበር ሲሆን፣ በጤና ድርጅቶች በተደረገ ...

Read More »

የኖርዌይ ኤምባሲ ዜጎቹ በኦሮሚያ ሲንቀሳቀሱ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳሰበ

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፥ 2008) ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተቃዉሞ ጋር በተገናኘ መቀመጫዉን በኢትዮጵያ ያደረገዉ የኖርዌይ ኤምባሲ፣ ዜጎቹ በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ከተሞች በሚያደረጉት እንቀሰቃሴ ላይ ጥንቃቄን እንዲያደርጉ ሰኞ በድጋሚ አሳስቧል። ተቃውሞው ከቅርብ ጊዜ ተቃውሞ ረገብ ያል ቢመስልም በማንኛውም ሰአት በድጋሚ ሊከሰትና የደህንነት ስጋት ሊያጋጥም ይችላል ሲል ኤምባሲዉ ገለጿል። በዚሁ ክልል አሁንም ድረስ አለመረጋጋት መኖሩን የገለጸዉ ኤምባሲዉ ዜጎቹ ሊያደርጓቸዉ ያሰቧቸዉን ጉዞዎች ...

Read More »

በኢትዮጵያ የምግብ ነክ ሸቀጣሸቀጦች የዋጋ ግሽበት ማሻቀቡን የማእከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ

ኢሳት (ታህሳስ 26 ፥ 2008) በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለዉን የድርቅ አደጋ ተከትሎ የሀገሪቱ የምግብ ነክ ሸቀጣሸቀጦች የዋጋ ግሽበት ከ11.5 በመቶ ወደ 12.1 በመቶ ማሻቀቡን የማእከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ሰኞ አስታወቀ። ወተትና ፓስታን ጨምሮ በተለያዩ የምግብ ዉጤቶች ላይ በየእለቱ የዋጋ ጭማሪ እየተመዘገበ መምጣቱንም መንግስታዊ ተቋሙ በወርሃዊ ሪፖርቱ አመልክቷል። በተለይ በስድስት ክልሎች ጉዳትን እያደረሰ የሚገኘዉ የድርቅ አደጋ በሀገሪቱ የምግብ ነክ ሸቀጣሸቀጦች ዋጋ እንዲንር በማድረግ ...

Read More »

በኦሮሚያ የመለስ ፓርኮችና የአደባባይ ፎቶግራፎች ተቃጠሉ

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፣ 2008) በኦሮሚያ ክልል ከማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ የተነሳው ተቃውሞ ሰሞኑን እንደገና አገርሽቶ በተለይም በምስራቁ የአገራችን ክፍል ከፍተኛ አለመረጋጋት መከሰቱን ከስፍራው የሚወጡ ዘገባዎች አመለከቱ። በምዕራብ ሃረርጌ ዞን ሂርና ከተማ እና በምስራቅ ሃረርጌ ዞን በደኖ ወረዳዎች በህወሃት/ኢህአዴግ ታጣቂዎችና በነዋሪው ህዝብ መካከል ከፍተኛ ግጭትና ፍጥጫ እንደነበር የአይን እማኞች ከስፍራው ለኢሳት ተናግረዋል። በበደኖና በሂርና አርብ የጀመረው ተቃውሞው እስከዛሬ ሰኞ ድረስ ...

Read More »

በጋምቤላ ክልል 9 የልዩ ሃይል አባላት ከእነሙሉ ትጥቃቸው ሸማቂ ቡድንኑ መቀላቀላቸው ተሰማ

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፥ 2007) የጋምቤላ ልዩ ሃይል አባላት ከእነሙሉ ትጥቃቸው የህወሃትን መንግስት በመክዳት ተቃዋሚዎችን መቀላቀላቸው ከአገር ቤት የደረሰን ዜና አመለከተ። የልዩ ሃይል አባላቱ የታጠቁትን የጦር መሳሪያ በመያዝ የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ጥምረት ግንባር የተባለው ሸማቂ ቡድን መቀላቀላቸውየኢሳት ምንጮች ከአገር ቤት ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች ብዛት ያላቸው የስርዓቱ መከላከያ ሃይል አባላት ስርዓቱን እየከዱ ሸማቂ ቡድኑን እየተቀላቀሉ ናቸው ተብሏል። የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ጥምረት ...

Read More »

በዲላ ዩንቨርስቲ በተከሰተው ግድያ የተነሳ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፣ 2008) ባለፈው ሐሙስና ቅዳሜ ጠዋት በዲላ ዩንቨርስቲ በእጅ በተወረወረ ቦምብ ጥቃትና በስለት ተወግተው 4 ተማሪዎች መሞታቸውን ከዲላ የአይን እማኞች ለኢሳት ተናግረዋል። ከተጎጂዎቹ ውስጥ በቦምብ ጥቃት የሞቱት በተለምዶ “ሰመራ” ተብሎ በሚጠራው ካምፓስ የሚኖሩ ሁለት ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ከ10 የማያንሱ ተማሪዎች ደግሞ በቦምብ ፍንዳታውና በጩቤ ተጎድተው በዲላ ሬፈራል ሆስፒታል ህክምና እያገኙ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። በተጨማሪውም ባለፈው ቅዳሜ ጠዋት ...

Read More »

የመንግስት ወታደሮች በኦሮምያ የሚፈጽሙትን ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እንደቀጠሉ ነው

ታኀሳስ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለተከታታይ ሳምንታት በኦሮምያ የተደረገው ህዝባዊ ተቃውሞ ደም አፋሳሽ ሆኖ ቀጥሏል። የመንግስት ወታደሮች ያለርህራሄ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እየወሰዱ ነው። እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መንገድ የተገደሉ ዜጎችን ምስል በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን ማየት የተለመደ ክስተት ሆኗል። መንግስት የሚወስደው ከልክ ያለፈ እርምጃ ተቃውሞን ከመባባስ ውጭ ሊገታው አልቻለም። በምእራብ ሃረርጌ በቆቦ ከተማ፣ ...

Read More »

በዲላ ዩኒቨርስቲ ግጭቱ ተባብሶ ሊቀጥል እንደሚችል ተማሪዎች ስጋታቸውን ገለጹ

ታኀሳስ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሶስት ቀናት በፊት በዲላ ዩኒቨርስቲ ምሽት ላይ በተመሳሳይ ሰአት በፈነዱ 4 ቦንቦች አንድ ተማሪ ወዲያውኑ ሲሞት፣ አንደኛው ሆስታል ከገባ በሁዋላ መሞቱ መዘገቡ ይታወሳል። ፍንዳታውን ተከትሎ 10 ተማሪዎች በጩቤ የተወጉ ሲሆን፣ አንዳንድ ተማሪዎች ለዘጋቢያችን እንደገለጹት ጉዳቱን ያደረሱት የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላት አለመሆናቸውን ተናግረዋል። በፍንዳታው አንድ አዳማና ሌላ ደብረብርሃን ልጅ ሲገደሉ፣ አንድ አርባ ...

Read More »