.የኢሳት አማርኛ ዜና

በሃረማያ ዩንቨርስቲ ዳግም የተቀሰቀሰውን አመጽ ተከትሎ ተማሪዎችና አርሶ-አደሮች ክፉኛ ተደበደቡ

ኢሳት (ጥር 3 ፥ 2008) ሰኞ ሃረማያ ዩንቨርስቲ ዳግም የተቀሰቀሰውን የተማሪዎችን ተቃውሞ ተከትሎ ዩንቨርስቲው ትምህርት ማቋረጡን እማኞች ገለጡ። የጸጥታ ሃይሎች በተማሪዎች ላይ እየወሰዱ ባለው የሃይል እርምጃ በርካታ ተማሪዎች መደብደባቸውንና ቁጥራቸው ሊታወቅ ያልቻለ ተማሪዎች ለእስር መዳረጋቸው ታውቋል። ከዚህ በፊት ለእስር የተዳረጉ ተማሪዎች እንዲፈቱ ጥያቄን ማቅረብ የጀመሩ በርካታ ተማሪዎች የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች የሚወስዱትን የሃይል እርምጃ እንዲቆም ጥያቄ ማቅረባቸው ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ ...

Read More »

የኖርዌይ ኤምባሲ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው ተቃውሞ በማገርሸቱ ዜጎች የጥንቃቄ እርምጃን እንዲወስዱ አሳሰበ

ኢሳት (ጥር 3 ፥ 2008) መቀመጫውን በኢትዮጵያ ያደረገ የኖርዌይ ኤምባሲ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ዳግም በማገርሸቱ ምክንያት ዜጎች በክልሉ በሚያድርጉት ጉዞ ላይ የጥንቃቄ እርምጃን እንዲወስዱ አሳስቧል። የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ በቅርበት የምትከታተለው ኖርዌይ እየተካሄደ ያለው ተቃውሞ የጸጥታ ስጋት ሊሆን እንደሚችል አስታውቋል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለስልጣናት በቅርቡ ለኤምባሲ ተወካዮች በሰጡት ማብራሪያ ተቃውሞው በቁጥጥር ስር ዉሏል ሲሉ ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል። ይሁንና ...

Read More »

በጅማ ዩኒቨርስቲ ቦንብ ሲፈነዳ በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ ደግሞ ተማሪዎች ተደብደቡ

ጥር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ተማሪዎች እንደገለጹት ፣ ትናንት ምሽት ላይ መብራት ከጠፋ በሁዋላ የእጅ ቦንብ የተወረወረ ሲሆን፣ ፍንዳታውን ተከትሎ የመንግስት ታጣቂዎች ወደ ተማሪዎች ማደሪያ ክፍል እየገቡ ደብድበዋቸዋል። በፍንዳታው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። ተማሪዎቹ ፍንዳታውን ያደረሱት ወታደሮች ናቸው ይላሉ። ፍንዳታው ተቃውሞ ሊያሰሙ ይችላሉ በሚሉዋቸው ተማሪዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ሆን ብሎ የተቀናበረ ...

Read More »

በምስራቅ ሀረርጌ የተከሰተው ረሃብ የህልውና ስጋት መደቀኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል

ጥር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከፍተኛ ረሃብ ገብቷል የሚሉት ነዋሪዎች፣ አስቸኳይ እርዳታ በፍጥነት ካልደረሰላቸው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ሊያልቅ ይችላል። በገጠር አካባቢ የሚኖረው ህዝብ ወደ ከተሞች መሰደድ ጀምሯል። ምንጮችና ወንዞች በመድረቃቸው ውሃ ለማግኘት አልተቻለም ሲሉ የውሃ እጥረት ለመሰደዳቸው ዋና ምክንያት መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። አንዳንድ አርሶአደሮች ከብቶቻቸውን እየሸጡ ችግሩን ለማሳለፍ እየሞከሩ ቢሆኑም፣ የከብቶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ...

Read More »

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ሁሉም ዜጋ በኅብረት እንዲቆም አገራዊ ጥሪ አቀረበ

ጥር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያን ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ተግዳሮቶችን ለመቀየር እያንዳንዱ ዜጋ ይህንን ዘረኛ ስርዓት ለመጣል በአንድነት በፅናት መታገል እንደሚገባው ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በአቋም መግለጫውን ጠቅሷል። “መብታቸው ለተረገጠ፤ ለተገፉ፤ አድሎ ለተፈጸመባቸው፤ ስብዓዊ መብታቸው ለተገፈፉ ዜጎች መቆም ያለብን ወቅት ላይ ነን። መደራጀትና የትኩረት አቅጣጫችንን የጋራ በሆኑ እሴቶችና ግቦች ላይ ማተኮር ያለብን ጊዜ ቢኖር ዛሬ ነው። እያንዳንዳችን ...

Read More »

ህወሃት/ኢህአዴግ የዘር-ፍጅት በመቀስቀስ ላይ መሆኑን ታማኝ ምንጮች ገለጹ

ኢሳት (ጥር 3 ፥ 2008) በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ ሁለት ወራት ባስቆጠረበት በአሁኑ ወቅት፣ የመንግስት የደህንነት ሃይሎች የዘር ፍጅት በመቀስቀስ የተቃውሞውን አቅጣጫ ለመቀየር በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውን ታማኝ የውስጥ ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። የዘር ፍጅት እቅዱ በኦሮሚያ ክልል በሚኖሩ የሌላ ብሄረሰብ ተወላጆች በተለይም በአማሮች ላይ የተነጣጠረና የተቀነባበረ ጥቃት በመሰንዘር፣ የሌላ አካባቢ ተወላጆች በስጋት ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ በማድረግ ሁኔታውን ወደ እርስ-በእርስ ግጭት ...

Read More »

ኬንያ በኢትዮጵያ ድንበር ተጨማሪ ወታደሮችን አሰማራች

ኢሳት (ጥር 2 ፣ 2008) በኢትዮጵያና የኬንያ ድንበር አካባቢ በሳምንቱ መገባደጃ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ ኬንያ ተጨማሪ ወታደሮችን በድንብር ዙሪያ አሰማራች። ከኢትዮጵያ የዘዘቁ ታጣቂዎች ቅዳሜ አንድ የኬንያ ተጠባባቂ ባልደርባን የገደሉ ሲሆን፣ በድርጊቱም በርካታ የቤት እንስሳትቶችም እንደተወሰዱ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ከኢትዮጵያ ግዛት ዘልቀው ገብተዋል የተባሉ ታጣቂዎች በአንድ ተሽከርካሪ ላይ የተኩስ እርምጃ በመክፈት አብዲ ኤደን የተባለ የሃገሪቱ ተጠባባቂ ሃይል ባልደርባ መገደሉን የማርሳቤት ...

Read More »

በኦሮሚያ የክልል ከተሞች የተቀሰቀሰው ተቃውሞ አሁንም እንደቀጠለ ነው

ኢሳት (ጥር 2 ፥ 2008) በተለያዩ የኦሮሚያ የክልል ከተሞች የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ሰኞ በምስራቅና በምዕራብ ሃረርጌ አካባቢዎች መቀጠሉ ተገለጠ። በመለስተኛ ከተሞች በተካሄደው በዚሁ ተቃውሞ፣ ነዋሪዎችና ተማሪዎች ለእስር የተዳረጉ ተማሪዎች በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥያቄ ማቅረባቸው ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል። በምዕራብ ሃረርጌ ጭሮ ከተማና አካባቢዋ ሰሞኑን የተቀሰቀሰው ተቃውሞ አለመርገቡንና ተመሳሳይ ተቃውሞዎች በምስራቅ ሃረርጌ በሚገኙ ከተሞች ሲካሄድ ማርፈዱም ታውቋል። በምዕራብ ሃረርጌ ሜዔሶ ወረዳና አካባቢው ...

Read More »

የአፋርና የሶማሌ ክልል በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ወደርሃብ ሊቀየር ይችላል ተባለ

ኢሳት (ጥር 2 ፥ 2008) በደቡብ የአፋርና የሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን የሚገኙ ቀበሌዎች ውስጥ ተከስቶ የሚገኘው የድርቅ አደጋ በቀጣዮቹ ሁለት ወራቶች ወደርሃብ ሊቀየር እንደሚችል አንድ አለም አቀፍ ተቋም አሳሰበ። በደረጃ ሶስት የድርቅ አደጋ ውስጥ ተፈርጀው የሚገኙት እነዚሁ አካባቢዎች አፋጣኝ እርዳታን ካላገኙ ወደ “ረሃብ” ደረጃ በሚመደበው ደረጃ አራት ሊሸጋገሩ ኣንደሚችሉ ድርጅቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለአስችኳይ የምግብ እርዳታ የተጋለጡ ሰዎችን ቁጥር 10.2 ...

Read More »

በአርባምንጭ ከተማ ወጣቶች  በህወሃት/ ኢህአዴግ ሃይሎች በገፍ እየታደኑ በመታሰር ላይ ናቸው ተባለ

ኢሳት (ጥር 2 ፥ 2008) በአርባምንጭ ከተማ ብዙ ወጣቶች የግንቦት 7 አባል ናችሁ በሚል ሰበብ ተጠርጥረው ዕርቃናቸውን ግርፋትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸሙባቸው ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። 20 አመት እድሜ ላይ የሚገኙ ዮሴፍ ይስሃቅና፣ እንዳሻው ወንድይፍራው ከዚህ በፊት በአርባምንጭ ከተማ ከጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ እያንዳንዳቸው በ2ሺ ብር ዋስትና እንደተለቀቁ፣ “ወያኔን ሰድበዋል፣ ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ግንኙነት አላቸው” በሚል ሰበብ እንደተደበደቡ በስፍራው ...

Read More »