ሚያዚያ ፮(ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በባህርዳሬዎች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት አለው፤ በታሪካዊነቱ ብቻ ሳይሆን ፣ በጣፋጭነቱም ይታወቃል፡፡ በ1962 ዓም የተቁዋቁዋመው እና ለ50 አመታት ተወዳጅነቱን ጠብቆ የዘለቀው የመጀመሪያው ዳቦ ቤት የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበታል፡ ዳቦ ቤቱን የመሰረቱት ሃጅ አድጎይ መሃመድ ወይም በከተማው ህዝብ አጣራር አባ አድጎይ ዛሬ በህይወት የሉም፡፡ ቤተሰቦቻቸው ግን ድርጅቱን ይዘው በመዝለቅ እስካሁን ድረስ የከተማውን ህዝብ ዳቦ እየጋገሩ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
የፍርሃት ስሜት፣ ሁከት፣ አመጽ እንዲፈጠር የሚያነሳሳ ጽሁፍና የተንቀሳቃሽ ምስልን አሰራጭቶ የተገኘ ሰው በህግ የሚያስቀጣ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ
ኢሳት (ሚያዚያ 5 ፥ 2008) በኢትዮጵያ በአገልግሎት ላይ ያሉ የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልኮችን ለመመዝገብ በዝግጅት ላይ የሚገኘው መንግስት አመጽ የሚያነሳሳ ወይም ጹሁፍን ማስተላለፍን ጨምሮ ሌሎች ድርጊቶችን በህግ የሚያስቀጣ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ አቀረበ። ይኸው በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ረቂቅ አዋጅ ማንኛውም ሰው በህበረተሰቡ መካከል የፍርሃት ስሜት፣ ሁከት፣ አመጽ እንዲፈጠር የሚያነሳሳ ጽሁፍና የተንቀሳቃሽ ምስልን አሰራጭቶ ከተገኘ በህግ እንደሚቀጣ አመልክቷል። ከዚህ በተጨማሪም ማንኛውም ሰው ...
Read More »ከ20 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን የምግብ እርዳታ ጠባቂ መሆናቸውን ተመድ ገለጸ
ኢሳት (ሚያዚያ 5 ፥ 2008) በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ እየባሰና እየተስፋፋ በመቀጠል ከህዝቡ 1/5ኛው ወይንም 20 ሚሊዮን ያህሉ የምግብ እርዳታ ጠባቂ ማድረጉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገለጸ። በታህሳስ ወር ላይ በድርቅ ተጠቂ የነበሩት 429 ወረዳዎች ቢሆኑም በአሁኑ ወቅት የድርቅ ሰለባ የሆኑ ወረዳዎች ቁጥር በ 14 ጨርሞ 443 መድረሱንም የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን በመጥቀስ ብሉምበርግ ዘግቧል። በድርቁ በከፍተኛ ደረጃ የተጠቁ ወረዳዎች ቁጥር በ18 በመቶ ...
Read More »በኦሮሚያ ክልል በመንግስት ሃይሎች የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አለም-አቀፍ ትኩረት አለማግኘቱን ሂውማን ራይትስ ዎች ገለጸ
ኢሳት (ሚያዚያ 5 ፥ 2008) ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በኢትዮጵያ ጸጥታ ሃይሎች ቢገደሉም፣ አለም አቀፍ ማህበረሰቡ ዝምታን መምረጡ እንዳሳዘነው የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት (Human Rights Watch) ትናንት ባወጣው መግለጫ ገለጸ። በኦሮሚያ ክልል የታየው ተቃውሞ ከምርጫ 97 በኋላ ከተቀሰቀሱት የፖለቲካ ቀውሶች ትልቁ እንደሆነ የገለጸው የሰብዓዊ መብቶች ጠባቂ ድርጅት (Human Rights Watch)፣ ይህ ተቃውሞ ግን በአለም አቀፍ መድረክ ያገኘው ...
Read More »የድርቅ መከሰትን ተከትሎ ከ600 ሺ በላይ ዜጎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን ተመድ ገለጸ
ኢሳት (ሚያዚያ 5 ፥ 2008) በኢትዮጵያ በስድስት ክልሎች ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ መባባስን ተከትሎ ከ600ሺ በላይ ሰዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገለጸ። ድርቁ እያደረሰ ያለው ጉዳት እልባት ባለማግኘቱ ምክንያትም ህይወታቸውን ለመታደግ ሲሉ መኖሪያ ቀያቸውን እየለቀቁ የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ሊሄድ እንደሚችልም ተሰግቷል። በድርቁ ሳቢያ ከተፈናቀሉት ወደ 640ሺ ሰዎች መካከል አብዛኞቹ በአፋር፣ ሶማሊ እና አማራ ክልል የሚገኙ ሲሆን ከእነዚሁ መካከልም ...
Read More »የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ወደ 4.5 በመቶ እንደሚያሽቆለቁል ተነገረ
ኢሳት (ሚያዚያ 5 ፥ 2008) በ11 በመቶ እድገትን ያስመዘግባል ተብሎ የተጠበቀው የዘንድሮው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ወደ 4.5 በመቶ እንደሚያሽቆለቁል የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ረቡዕ ይፋ አደረገ። የመንግስት ባለስልጣናት ለተከታታይ አመታት እድገትን አሳይቷል ያሉት የኢኮኖሚ እድገት በተያዘው አመት በሁለት አህዝ እድገትን ያስመዘግባል ሲሉ መግለጻቸው ይታወሳል። ይሁንና በአለም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ዙሪያ አዲስ ሪፖርትን ያወጣው የገንዘብ ተቋሙ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ...
Read More »በደሴ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ የትግል ጥሪ ወረቀቶች ተበተኑ
ሚያዚያ ፭(አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወጣቶች ትናንት ምሽት በተለያዩ የደሴ ከተማ አካባቢዎች የበተኑት ወረቀት የከተማው ህዝብ ትኩረት መሳቡን ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወጣቶች ተናግረዋል፡፡ የትግል ጥሪ ወረቀቶች፣ ህዝቡ ለመብቱ እንዲነሳ፣ በወልቃይት ጥያቄ ዙሪያ የደሴ ህዝብ ጥያቄውን ከሚያቀርቡ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ጋር በጋራ እንዲቆም የሚያሳስቡ ናቸው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ህዝብ በብዛት ይገኝባቸዋል በተባሉ ቦታዎች፣ በአራዳ፣ መናፈሻ፣ መላ፣ መናሃሪያ ...
Read More »ከአምስት እጅ አንዱ ኢትዮጵያዊ በከፍተኛ ረሃብ መጠቃቱ ይፋ ሆነ
ሚያዚያ ፭(አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ብሉምበርግ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ በረሃብ የተጠቁት ኢትዮጵያዊያን ቁጥር ቀድሞ ከተገለጠው 10 ሚሊዮን በእጥፍ ጨምሮ 20 ሚሊዮን ደርሶአል፡፡ ይህ አሃዝ በምግብ ለስራ የታቀፉትና የምግብ እርዳታ የሚሰፈርላቸውን 8 ሚሊዮን ዜጎች እንዲሁም፣ በከተሞች በምግብ እጥረት የተጠቁትን 10 ሚሊዮን ዜጎች አይጨምርም፡፡ በድርቅ ከተጎዱ 443 ወረዳዎች መካከል 219 ወረዳዎች ከፍተኛ የሆነ የምግብ ችግር አጋጥሞአቸዋል፡፡ ከፍተኛ የምግብ ...
Read More »የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ ከአምናው ጋር ሲነጻጸር ከግማሽ በታች እንደሚያሽቆለቁል አይ.ኤም.ኤፍ. አስታወቀ
ሚያዚያ ፭(አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በምህጻረ ቃሉ አይ ኤም ኤፍ ከሰሃራ በታች ያሉ አገራት በያዝነው ዓመት ላይ የኤኮኖሚ እድገታቸው እንደ ሚያሽቆለቁል ገልጾአል፡፡ ድርጅቱ ድርቁን ተከትሎ ኤኮኖሚያቸው ክፉኛ ከሚጠቁ አገራት ተርታ ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ተጎጂ አገር መሆኗንና ካለፈው ዓመት ካስመዘገበችው እድገት ከግማሽ በታች በመውረድ 4.5% ከመቶ እንደምታስመዘግብ ገልጾአል፡፡ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የነዳጅ ላኪ የአፍሪካ አገራት የዓለም ...
Read More »በኢትዮጵያ 84ሺህ ብቻ የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎች መኖራቸውን CNN ዘገበ
ዜና (ሚያዚያ 5 ፥ 2008) በአፍሪካ ባሉት 97 ሚሊዮን ህዝብ ቁጥር በአህጉሪቱ ከናይጀሪያ ቀጥላ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፣ 84ሺህ የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎች ብቻ እንዳሏት ተገለጠ። በጉዳዩ ዙሪያ ልዩ ዘገባን ያቀረበው ሲኤንኤን (CNN) የቴለቪዥን ጣቢያ ሃገሪቱ ከውጭ በሚገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ 35 በመቶ ታክስን እንደምታስከፍልም አመልክቷል። አብዛኞቹ ተሽከርካዎች ከውጭ ሃገር የገቡ መሆናቸውን ያወሳው የቴለቪዥን ጣቢያው በአሁኑ ወቅት 84ሺህ ተሽከርካሪዎች መኖራቸውን ባቀረበው ሪፖርት ...
Read More »