ኢሳት (ሃምሌ 21 ፥ 2008) በሚያዚያ ወር በጋምቤላ ክልል በደቡብ ሱዳን ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ተፈጽሟል በተባለው ጥቃት ታፍነው ከተወሰዱ ህጻናት መካከል 55 የሚሆኑት አሁንም ድረስ አለመለቀቃቸው ተገለጠ። የኢትዮጵያ መንግስት በደቡብ ሱዳን መንግስት በበኩሉ ሊካሄድ በነበረው ድርድር ታፍነው ከተወሰዱት ወደ 146 ህጻናት መካከል 91 የሚሆኑት ብቻ መለቀቃቸውን የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) አስታውቋል። በህጻናቱ መታገት ስጋቱን ሲገልጽ የቆየው ድርጅቱ የተለቀቁ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
በወልቃይት የማንነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የሚጠይቅ ህዝባዊ ትዕይንት በጎንደር እንደሚካሄድ አስተባባሪዎቹ ገለጹ
ኢሳት (ሃምሌ 21 ፥ 2008) የወልቃይት ህዝብ የማንነት ጥያቄ ያነሱ የኮሜቴ አባላት እንዲፈቱና የወልቃይት ህዝብ የማንነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የሚጠይቅ ህዝባዊ ትዕይት የፊታችን እሁን በጎንደር ከተማ እንደሚካሄድ አስተባባሪዎቹ ለኢሳት ገለጹ። ለሚመለከተው አካል ከ72 ሰዓታት በፊት ማሳወቃቸውንም ገልጸዋል። ሰልፉ በማናቸውም ሁኔታ እንዳማይቀር አረጋግጠው፣ “አትወጡም ብለው ቢተኩሱብን፣ እኛም በተኩስ ምላሽ እንሰጣለን በማለት ከሰልፉ ምድራዊ ሃይል እንደማይገታቸው አሳውቀዋል። ሃምሌ 5 ቀን 2008 የወልቃይት ...
Read More »7 የቤተሰብ አባላት በምግብ መመረዝ መሞታቸው ተነገረ
ኢሳት (ሃምሌ 21 ፥ 2008) በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በሮቤ ወረዳ ሰባት የአንድ ቤተሰብ አባላት በምግብ መመረዝ ምክንያት መሞታቸውን የክልሉ ፖሊስ ሃሙስ አስታወቀ። የልጆች እናት የሆኑትና ስማቸው ያልተጠቀሰው እማወራ በከተማዋ ከሚገኝ አንድ ሱቅ የገዙት ነጭ ዱቄትና እርሾ ለቤተሰብ አባላቱ ሞት ምክንያት መሆኑን የክልሉ ባለስልጣናት ዋቢ በማድረግ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የልጆቹ እናት ዱቄቱን በእርሾው አዘጋጅተው (አቡክተው) ካደሩ በኋላ በተረፈው እርሾ ...
Read More »በአዲስ አበባ የኮሌራ በሽታ መስፋፋቱን ተከትሎ ከ800 የሚበልጡ የምግብና የመጠጥ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ተዘጉ
ኢሳት (ሃምሌ 21 ፥ 2008) በአዲስ አበባ ከተማ በመስፋፋት ላይ ያለውን የኮሌራ በሽታ ስርጭት ተከትሎ በመዲናይቱ የንጽህና ጉድለት ታይቶባቸዋል የተባሉ ከ800 በላይ የምግብና የመጠጥ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ተዘጉ። የከተማዋ የጤና ቢሮ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ባካሄደው ዘመቻ በታሸጉት አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥ ሲሰሩ የነበሩ በርካታ ሰራተኞች በበሽታው ተይዘው መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ገልጿል። ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ...
Read More »በጎንደር ለእሁድ የተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ እንደማይታጠፍ ነዋሪዎች አስታወቁ
ሐምሌ ፳፩ ( ሀያ አንድ ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጋር በተያያዘ በሰሜን ጎንደር የተነሳውን ህዝባዊ አመጽ ለማብረድ ገዢው ፓርቲ የተለያዩ የማዘናጊያ ስልቶችን ቢጠቀምም፣ በህዝቡ ውስጥ ያለው ስሜት ግን ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍ ማለቱን ዛሬ በጎንደር መድሃኒያለም ቤተክርስቲያን የተሰበሰቡት የኮሚቴ አባላትና በስብሰባው ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በመጪው እሁድ ሃምሌ 24፣ 2016 ከጠዋቱ 2 ሰአት ...
Read More »በርሃብ አድማ ላይ የሚገኙት እነ አቶ በቀለ ገርባ ራሳቸውን ከሳቱ በሁዋላ ፈሳሽ ምግብ ( ግሉኮስ) ተተከለላቸው
ሐምሌ ፳፩ ( ሀያ አንድ ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ ሌሎች ዘጠኝ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ለቀናት ያካሄዱትን የረሃብ አድማ ተከትሎ ራሳቸውን የሳቱ ሲሆን፣ ወደ ሆስፒታል ሳይወሰዱም የእስር ቤቱ የህክምና ክፍል በእያንዳንዳቸው እጅ ላይ ፈሳሽ ምግብ ( ግሉኮስ) እንደተከለላቸው ታውቋል። የአቶ ደጀኔ ጣፋ ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ አሰለፈች ሙላቱ እንደገለጹት፣ እስረኞቹ ለሳምንት ያክል ምግብ ባለመብላታቸው ...
Read More »በአማራ ክልል የሚሰሩ ባንኮች ለክልሉ ተወላጆች ተፈላጊውን ብድር እንደማያመቻቹ ተነገረ፡፡
ሐምሌ ፳፩ ( ሀያ አንድ ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በክልሉ ውስጥ ለሚካሄዱ የኢንዱስትሪ ግንባታዎች ባንኮች ተገቢውን የብድር አገልግሎት እንዳይሰጡ በተዘዋዋሪ ስለሚከለከሉ ክልሉ እንደ አዋሳኝ ክልሎች የኢንዱስትሪ ዕድገቱ የተፋጠነ እንዳይሆን መደረጉ ቁጭት እየፈጠረባቸው መሆኑን ከፍተኛ የባንክ ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ ከሁሉም ክልሎች ከፍተኛ የቁጠባ ገንዘብ የሚከማቸው በአማራ ክልል ውስጥ ቢሆንም ከተከማቸው ውስጥ በብድር የሚቀርበው ግን ሃያ በመቶ ብቻ መሆኑን ...
Read More »መከላከያ ሰራዊት በቦረና ሚኦ ወረዳ ነዋሪዎች ላይ ተኩስ ከፍቶ አንድ ሰው ሲገድል ሶስት አቆሰለ
ኢሳት (ሃምሌ 20 ፥ 2008) በቦረና ዞን ሚዖ ወረዳ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በህዝብ ላይ በከፈቱት ተኩስ ሶስት ሰዎች መቁሰላቸውን የአይን ምስክሮች ለኢሳት ገለጹ። ማክሰኞ ዕለት በአካባቢው የመብት ጥያቄ በአደባባይ መነሳቱን ተከትሎ ረቡዕ ከተማዋን የተቆጣጠሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በእርቀት ተኩስ አንዲት የመንገድ ላይ ቸርቻሪም ሰለባ መሆኑ ታውቋል። ማክሰኞ ዕለት በሚዖ ወረዳ ኩሉቡማ ከተማ ህዝብ አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን ገልጿል ፥ ጥያቄም አቅርቧል። ...
Read More »በስድስት ክልሎች የሚገኙ 26 ወረዳዎች ወደ ረሃብ ደረጃ መሸጋገራቸው ተነገረ
ኢሳት (ሃምሌ 20 ፥ 2008) በኢትዮጵያ በድርቅ በተጎዱ አካባቢዎች ያለው ሁኔታ መባባስን ተከትሎ በሁለተኛ ደረጃ ተመድበው የነበሩ 26 ወረዳዎች ወደ ረሃብ ደረጃ ሊሸጋገር ወደሚችለው አንደኛ ደረጃ መሸጋገራቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ። ወደ አንደኛ ደረጃ የተሸጋገሩት እነዚሁ ወረዳዎች ተላላፊ በሆኑ በሽታዎች ጭምር ክፉኛ ጉዳት ይደርስባቸዋል ተብሎ ስጋት መኖሩን ድርጅቱ በሃገሪቱ ስላለው የድርቅ ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት አስፍሯል። በስድስት ክልሎች ተከስቶ ያለው ...
Read More »በኢትዮጵያ የብሊሃርዚያ በሽታ ስርጭት አሳሳቢ ነው ተባለ
ኢሳት (ሃምሌ 20 ፥ 2008) ኢትዮጵያ ካላት 90 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ ህዝቦቿ ወደ 23 ሚሊዮን አካባቢ የሚሆነው የብልሃርዚያ በሽታ ህክምናን የሚፈልግ እንደሆነና የበሽታው ስርጭትም አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን የአለም ጤና ድርጅት አስታወቁ። የብልሃርዚያ በሽታ በአለማችን ካልጠፋባቸው ጥቂት ሃገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ስትሆን የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር 14 ሚሊዮን ታብሌት ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ መጓጓዙን የአለም ጤና ድርጅትን ዋቢ በማድረግ አፍሪካ ኒውስ ማክሰኞ ዘግቧል። ...
Read More »