ኢሳት (የካቲት 23 ፥ 2009) በመገንባት ላይ ባለው የአባይ ግድብ ላይ ጥቃትን ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ የቤኒሻንጉል ነጻነት ንቅናቄ (ቤህነን) 13 ታጣቂዎች መገደላቸውን መንግስት ገለጸ። በተወስደባቸው ዕርምጃ ከተገደሉት ታጣቂዎች በተጨማሪ ሰባቱ ወደ ጎረቤት ሱዳን ከሸሹ በኋላ ለኢትዮጵያ ተላልፈው መሰጠታቸውንና የንቅናቄው አባላት መነሻቸውን ከኤርትራ እንዳደረጉ የመንግስት ቃል አቀባይ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዘዲግ አብርሃን ዋቢ በማድረግ አሶሼይትድ ፕሬስ ዘግቧል። ይሁንና የኤርትራ መንግስት ጥቃት ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን ያደረጉት ስምምነት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም ሲል የሱዳን አማጺ ቡድን አስታወቀ
ኢሳት (የካቲት 23 ፥ 2009) ኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን መንግስት ሰሞኑን ያደረጉት ሰምምነት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል በሪክ ማቻር የሚመራው አማጺ ቡድን ውስጥ በአባልነት የሚገኝ አንድ አንጃ ገለጸ። የኑዌር ጎሳዎች በአብዛኛው እንደሚወክል የሚነገርለት የሱዳን ህዝቦች የነጻነት ንቅናቄ ተቃውሞ አንጃ በደቡብ ሱዳን ሰላም በሌለበት ሁኔታ ሁለቱ ሃገራት የደረሱት ስምምነት ተፈጻሚ እንደማይሆን የአንጃው አመራሮች መግለጻቸውን ራዲዮ ታማዙጂ የተሰኘ ጣቢያ ዘግቧል። የአንጃው ምክትል ...
Read More »በህገወጥ መንገድ ወደ ሞዛምቢክ ገብተዋል የተባሉ 36 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ
ኢሳት (የካቲት 23 ፥ 2009) በህገወጥ መንገድ ወደ ሞዛምቢክ ገብተዋል የተባሉ 36 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሃገሪቱ የኢሚግሬሽን መምሪያ አስታወቀ። ስደተኛ ኢትዮጵያውያኑ በሞዛምቢክ ሰሜናዊ ግዛት በሆነው የናምፑላ አስተዳደር በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ እንዳሉ በሰው ጥቆማ ሊያዙ መቻላቸውን የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የግዛቲቱ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ዘካሪያስ ናኩቴ የኢሚግሬሽን የጸጥታ አባላትና የግዛቲቱ ፖሊስ በጋራ በመኖሪያ ቤቱ ላይ ባካሄዱት ከበባ ኢትዮጵያውያኑ በሰላም ...
Read More »በሶማሌ ክልል የከፋ የምግብ እጥረት ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ተመድ ገለጸ
ኢሳት (የካቲት 23 ፥ 2009) በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል የምግብ እርዳታ ለማግኘት በ24 መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ተሰባስበው በሚገኙ ሰዎች መካከል እየደረሰ ያለው የከፋ የምግብ እጥረትና ጉዳት በአለም አቀፍ ደረጃ ከተቀመጠው አህዝ በሶስት እጅ መብለጡ ስጋት እንዳሳደረበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይፋ አደረገ። በክልሉ እየተባባሰ የመጣውን የድርቅ አደጋ ተከትሎ የፌዴራልና የክልሉ መንግስት ከ20ሺ የሚበልጡ ነዋሪዎች በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ እንዲሰባሰቡ ማድረጋቸው ይታወሳል። ይሁንና እርዳታ ...
Read More »ህወሃት ወደ አዲስ አበባ እየገፋ በመጣበት ወቅት የመንግስት መቀመጫን ከአዲስ አበባ ለማንሳት ክርክር መደረጉ ተገለጸ
ኢሳት (የካቲት 23 ፥ 2009) የህወሃት/ኢህአዴግ አማጺያን ወደ አዲስ አበባ እየገፉ በመጡበት ወቅት የመንግስት መቀመጫ ከአዲስ አበባ ለማንሳትና ወደ ደቡብ ወይንም ምስራቅ ለመውሰድ ክርክር መደረጉን ተገለጸ። በቀድሞ የኢትዮጵያ መንግስትና በአማጺያን መካከል የተደረገው ድርድርም በአሜሪካ ጣልቃገብነት እንደከሸፈ ይፋ ሆኗል። ይህ የተጋለጠው በለንደን በተካሄደው ድርድር የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን በመምራት በሂደቱ ተዋናይ በነበሩት በጠ/ሚኒስተር ተስፋዬ ዲንቃ መጽሃፍ ላይ ነው። በዚህ ሳምንት ለንባብ የበቃውና ...
Read More »በአብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሆኑ 500 ሺ ስደተኞች በሱዳን እንደሚገኙ የአውሮፓ ህብረት አስታወቀ
ኢሳት (የካቲት 22 ፥ 2009) አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሆኑ ወደ 500ሺ አካባቢ የሚጠጉ የኤርትራና የሶማሊያ ስደተኞች በሱዳን እንደሚገኙ የአውሮፓ ህብረት አስታወቀ። ሰሞኑን ሱዳን በኢትዮጵያውያን እና ኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ ፈጽማዋለች የተባለውን ኢሰብዓዊ ድርጊት ተከትሎ ለሃገሪቱ የሚሰጠውን የስደተኞች የገንዘብ ድጋፍ እንዲያቋርጥ የተጠየቀው ህብረቱ ለሃገሪቱ እስካሁን ድረስ የለቀቀው ድጋፍ አለመኖሩን ገልጿል። የሱዳን የድንበር ተቆጣጣሪ ሃይሎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጀምሮ ወደ ሃገሪቱ ድንበርን እያቋረጡ የሚገቡ ...
Read More »በጋምቤላ ክልል በሰፋፊ የእርሻ ልማት ለመሰማራት የሚፈልጉ ባለሃብቶች በባንክ የተቀመጠ 7.5 ሚሊዮን ብር ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ
ኢሳት (የካቲት 22 ፥ 2009) በጋምቤላ ክልል ለሰፋፊ የእርሻ ልማት ስራ ሲሰጥ በቆየው ብድር በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ኪሳራ የደረሰበት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዘርፉ መሰማራት የሚፈልጉ ባለሃብቶች በትንሹ 7.5 ሚሊዮን ብር ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው አዲስ መመሪያን ተግባራዊ አደረገ። ባንኩ ባለፉት ጥቂት አመታት በጋምቤላ ክልል ሲሰጥ በቆየው ብድር በርካታ ባለሃብቶች በተመሳሳይ መሬት ላይ ተደራራቢ ብድርን በመውሰድ ለብድር የተሰጠ ከሶስት ቢሊዮን ብር በላይ የገባበት ...
Read More »በአዲስ አበባ አንድ ጣሊያናዊን የገደሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል እየተደረገ ነው ተባለ
ኢሳት (የካቲት 22 ፥ 2009) ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በጥይት የተገደለ ጣሊያናዊ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትል እያደረገ መሆኑን ገለጸ። ስሙ ያልተገለጸው የ32 አመት ጣሊያናዊ የካቲት 18 ምሽት በከተማዋ ቦሌ ክፍለ ከተማ በአንድ የምሽት ክበብ በመዝናናት ላይ እንዳለ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ማለፉን በስፍራው የነበሩ እማኞች ለሃገር ውስጥ መገናኛ ተቋማት አስረድተዋል። ሟች ከጓደኞቹ ጋር ...
Read More »በአማራ ክልል ጎንደርና ባህርዳር “ኮማንድ ፖስት” ተጨማሪ ተጽዕኖ እያደረሰ መሆኑ ተነገረ
ኢሳት (የካቲት 22 ፥ 2009) በአማራ ክልል ከተቀጣጠለው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ወዲህ በከፍተኛ ልዩ ጥበቃ ውስጥ የሚገኙ የጎንደርና የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች በኮማንድ ፖስቱ ተጨማሪ ተጽዕኖ እየተደረገባቸው መሆኑን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። በዚሁም የባህርዳር ከነማና የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ቡድን ደጋፊዎች ዝርዝር ለኮማንድ ፖስቱ መመሪያ ተላልፏል። በሌላ በኩል በወህኒ ቤት የሚገኙ እስረኞችን በአማራ ክልል ቴሌቪዥን መቅረጽ ተጀምሯል። በሃምሌ 2008 ዓም መጀመሪያ በጎንደር የተነሳውና ...
Read More »ታጋይ ጎቤ መልኬ መስዋቱ ታወቀ
የካቲት ፳፪ ( ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የነጻነት አርበኛው ታጋይ ጎቤ መልኬ ከሃምሌ 5 ቀን 2008 ዓም ጀምሮ የህወሃት ኢህአዴግ አገዛዝን በመሳሪያ ሲፋለም ቆይቶ፣ መሰዋቱን ምንጮች ገልጸዋል። በጀግንነቱ የብዙ ነጻነት ወዳድ ኢትዮጵያውያንን ቀልብ የገዛው የ70 አመቱ ታጋይ ጎቤ፣ በእሱ የሚመራው ሃይል ከህዳር 16 ቀን 2009 ዓም ጀምሮ በገዢው ፓርቲ ወታደሮች ላይ በተዳጋጋሚ ሲያደርስ በነበረው ጥቃት ከፍተኛ ...
Read More »