.የኢሳት አማርኛ ዜና

በነርሶቸ እንዘላልነት የአንድ ወላድ ህይወት አለፈ

የካቲት ፳፰ ( ሃያ ስምንት )ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ ቀጨኔ ልዩ ስሙ ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ ህዳሴ በሚባል ጤና ጣቢያ ውስጥ ነርሶች ለወላዷ የምጥ መርፌ ከወጉዋት በሁዋላ ፣ ከወላዱዋ ርቀው ሲጫውቱ ቆይተው ሲመለሱ ህይውቱዋ አልፎ ያገኙዋት ሲሆን፣ በዚህ ድርጊት የተብሳጩት የአካባቢው ነዋሪዎቸ የጤና ጣቢያውን በሮችና መሰኮቶች በድንጋይ ሰባብረዋል። ወላዱዋ ከቀኑ 8 ሰአት ላይ እንደገባችና ምሽት ...

Read More »

የትራምፕ አስተዳደር  ስደተኞችን በተመለከተ ለሁለተኛ ጊዜ ያስተላለፈው ውሳኔ በድጋሚ ከህግ አካላት ዘንድ ተቃወሞ ገጠመው

ኢሳት (የካቲት 28 ፥ 2009) የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ሰኞ ስደተኞችን በተመለከተ ለሁለተኛ ጊዜ ያስተላለፈውን ውሳኔ በድጋሚ ከህግ አካላት ዘንድ ተቃወሞ ገጠመው። ፕሬዚደንቱ በአዲስ መልክ ያወጡትን ውሳኔ የተቃወሞ አካላት ዕርምጃው አሁንም ቢሆን የሙስሊም ሃገራትን ሆን ብሎ ያነጣጠረ ነው ሲሉ ቅሬታን በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። በዚሁ አዲስ ውሳኔ መሰረት ስድስት ሃገራት ለሶስት ወር ተግባራዊ የሚሆን የጉዞ እገዳ የተጣለባቸው ሲሆን፣ ...

Read More »

ለአስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ተጋልጠው የሚገኙ ሰዎች በገንዘብ እጥረት የተነሳ የምግብ አቅርቦት እንደማያገኙ ተመድ ገለጸ

ኢሳት (የካቲት 28 ፥ 2009) በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ተጋልጠው የሚገኙ በሚለዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በገንዘብ እጥረት የተነሳ በቂ የምግብ አቅርቦት አለማግኘታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ። ለሃገሪቱ የሚያስፈልገው አለም አቀፍ ድጋፍ በወቅቱ ባለመገኘቱ ምክንያት በደቡብ ክልል የህክምና ባለሙያዎችን ማሰማራት አልተቻለም ያለው ድርጅቱ የድርቁ አደጋ ከመቼውም ጊዜ በላይ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የኢትዮጵያ መንግስት ከሁለት ወር በፊት ድርቁን ለመቋቋም ...

Read More »

በናይጀሪያ አቡጃ የሚገኝ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ እንዲዘጋ ለጊዜው ቢወሰንም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአማራጭነት ተጠቃሚ ነው ተባለ

ኢሳት (የካቲት 28 ፥ 2009) በናይጀሪያ አቡጃ ከተማ የሚገኝ አለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ለጊዜው እንዲዘጋ ቢወሰንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአማራጭነት የቀረበን አየር ማረሪያ ለመጠቀም ብቸኛ አየር መንገድ ሆኖ መቅረቡን የናይጀሪያ የአቪየሽን ባለስልጣናት አስታወቁ። በአቡጃ ከተማ የሚገኘው የናምዲ አዚክዌ አየር ማረፊያ ላይ የተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ወደ ከተማዋ አለም አቀፍ የበረራ አገልግሎትን የሚሰጡ 25 አየር መንገዶች በአማራጭነት የቀረበውን አየር ማረፊያ በመቃወም በረራ ...

Read More »

ለነጻነት በሚደረገው ትግል ኢትዮጵያውያን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ተጠየቀ

ኢሳት (የካቲት 28 ፥ 2009) ለነጻነት በሚደርገው ትግል ኢትዮጵያውያን በአቅማቸውና በሙያቸው አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ ጥሪ አቀረበ። በአራት ድርጅቶች በቅርቡ የተመሰረተው ሃገራዊ ንቅናቄ በዋሽንግተን ዲሲ  ከኢትዮጵያን ጋር ባካሄደው ውይይት በሀገሪቱ ያሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን መሰረት ያደረገ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጿል። የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ አርበኞች ግንቦት 7፣ የአፋር ህዝብ ፓርቲ፣  እና የሲዳማ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ በጋራ ...

Read More »

በሱዳን የሚኖሩ የሃይማኖት አባትና ሌሎች ስደተኞች ለኢትዮጵያ ተላልፈው ተሰጡ

ኢሳት (የካቲት 28 ፥ 2009) በሱዳን የጸጥታ ሃይሎች ለእስር ተዳርገው የነበሩ አንድ የኢትዮጵያ የሃይማኖት አባትና ሌሎች ሰዎች ለኢትዮጵያ ተላልፈው መሰጠታቸውን ጉዳዩን በመከታተል ላይ ያሉ አባላት ለኢሳት አሳታወቁ። የሃይማኖች አባቱ ቄስ ተገኝ በሱዳን የጸጥታ ሃይሎች ታፍነው ላለፉት 10 ወራቶች ያህል በእስር ላይ እንደነበሩ የተናገሩት እነዚሁ አካላት በሃገሪቱ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን የሃይማኖት አባቱን ጉዳት በመከታተል ላይ እንደነበር ከዜና ክፍላችን ጋር ...

Read More »

በሶማሊያ ከ100 በላይ ሰዎች በረሃብ ምክንያት መሞታቸውን ተገለጸ

ኢሳት (የካቲት 27 ፥ 2009) ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ በረሃብ ምክንያት ከ100 በላይ ሰዎች በሶማሊያ መሞታቸውንና የሟቾች ቁጥር እየጨመረ እንደሚካሄድ ስጋት መኖሩን የሃገሪቱ ባለስልጣናት ሰኞ ይፋ አደረጉ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ ኢትዮጵያን ጨምሮ በጎረቤት ሃገራት ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ የከፋ ችግር ከማስከተሉ በፊት የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ርብርብ እንዲያደርግ በድጋሚ አሳስቧል። በዚሁ የድርቅ አደጋ ተጠቂ በሆነችው ሶማሊያ ቤይ ተብሎ በሚጠራው ግዛት ...

Read More »

የዞን 9 ጦማሪያን ለ53ኛ ጊዜ ቀጠሮ ተሰጣቸው

ኢሳት (የካቲት 27 ፥ 2009) አቃቤ ህግ ባቀረበባቸው ይግባኝ ለ52ኛ ጊዜ ፍርድ/ቤት የቀረቡት የዞን 9 ጦማሪያን ውሳኔ ሳያገኙ ለ53ኛ ጊዜ ቀጠሮ እንደተሰጣቸው ታወቀ። ይግባኝ የተጠየቀባቸው ጦማሪያን በፍቃዱ ሃይሉ፣ ናትናዔል ፈለቀ፣ አቤል ዋበላ፣ አጥናፍ ብርሃኔ እንዲሁም ሶሊያና ሽመልስ (በሌለችበት) ተለዋጭ ቀጠሮ ለመጋቢት 11, 2009 ተሰጥቷቸዋል። ዓቃቤ ህግ የተከሳሾቹን ከእስር መፈታት በመቃወም ያቀረበው ይግባኝ ዕልባት ሳያገኝ ለ53ኛ ጊዜ በቀጠሮ ሲሸጋገር ከጦማሪያን አንዱ ...

Read More »

የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በ77 ግለሰቦች ላይ ክስ መሰረተባቸው

ኢሳት (የካቲት 27 ፥ 2009) የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና ነዳጅ ከጎረቤት ወደ ሃገር ውስጥ እንዳይገባ አድርገዋል የተባሉ 77 ግለሰቦች ክስ እንደተመሰረተባቸው አስታወቀ። ከተከሳሾቹ መካከል 12ቱ ኤርትራውያን ናቸው የተባሉ ሲሆን፣ ግለሰቦቹ የአርበኞች ግንቦት 7 አባል በመሆኑ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ተቋማትን ለማናጋት ሲንቀሳቀሱ ነበር ሲል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በክሱ ማመልከቱን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ተከሳሾቹ ከጥር 2 ቀን ...

Read More »

በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ረገጣን የገመገመው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመታዊ ሪፖርት ይፋ ሆነ

ኢሳት (የካቲት 27 ፥ 2009) የኢትዮጵያን የ2016 አም አጠቃላይ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ የገመገመው አመታዊ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር (State Department) ሪፖርት ይፋ ሆነ። እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2016 ዓም የኢትዮጵያ መንግስት የጸጥታ ሃይሎች በሰላማዊ ዜጎች ላይ ከልክ ያለፈ ሃይል እንደጠተቀሙ የገለጸው ይኸው ሪፖርት፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ መገደላቸውና በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን አመልክቷል። ሪፖርቱ፣ የህዝባዊ እምቢተኝነት ተቃውሞዎች የተደረጉት በአብዛኛው በኦሮሚያና አማራ ክልሎች መሆናቸውና፣ ይህኑም ...

Read More »