.የኢሳት አማርኛ ዜና

የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በጋምቤል ክልል ጥቃት ፈጽመው 28 ሰዎችን ሲገድሉ 43 ህጻናትን ጠልፈው መውሰዳቸው ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 6 ፥ 2009) ሰሞኑን ከደቡብ ሱዳን ድንበር በመዝለቅ በጋምቤላ ክልል ጥቃት የፈጸሙ ታጣቂዎች 28 ሰዎች መግደላቸውንና 43 ህጻናትን ዳግም አግተው መውሰዳቸውን መንግስት አረጋገጠ። የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት በፈጸሙት ጥቃት ከ100 የሚበልጡ ሰዎች መገደላቸውንና ወደ 125 አካባቢ የሚደርሱ ህጻናት ታፍነው መወሰዳቸው ይታወሳል። ይኸው ጥቃት ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በድጋሚ መፈጸሙንና በርካታ ሰዎች መሞታቸውን ኢሳትና ሌሎች የመገናኛ ብዙሃን ...

Read More »

በሴት ልጁ ላይ ግርዛት ፈጽሟል የተባለ ኢትዮጵያዊ ከ10 አመት የእስር ቅጣት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ተደረገ

ኢሳት (መጋቢት 6 ፥ 2009) ነዋሪነቱ በዚሁ በአሜሪካ የነበረ አንድ ኢትዮጵያዊ በሴት ልጁ ላይ ፈጽሞታል በተባለ ግርዛት ከ10 አመት የእስር ቅጣት በኋላ ሰኞ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ተደረገ። ነዋሪነቱ በጆርጂያ ግዛት የነበረው የ41 አመቱ ካሊድ አህመድ ከ10 አመት በፊት በሁለት አመት ህጻን ልጁ ላይ የፈጸመው ግርዛት በአሜሪካ ታሪክ የተከለከለና ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጸመ እንደነበር ኒው ዮርክ ታይምስ ጋዜጣ የፍርድ ቤት ውሳኔን ዋቢ ...

Read More »

በተለምዶ “ቆሼ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቁፋሮ የሚገኝ አስከሬን መጨመሩን ተከትሎ ሰዎች ወደቦታው እንዳይገቡ ታገዱ

ኢሳት (መጋቢት 6 ፥ 2009) በአዲስ ከተማ ለበርካታ ሰዎች ሞት ምክንያት በሆነውና በተለምዶ “ቆሼ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በየዕለቱ በቁፋሮ የሚገኝ አስከሬን መጨመሩን ተከትሎ ሰዎች ወደቦታው እንዳይገቡ ታገዱ። የቤተሰብ አባሎቻቸው የገቡበት ያልታወቁ የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው ቁፋሮን የማካሄዱ ስራ ተጓትቷል በማለት ቅሬታን እያቀረቡ መሆኑን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል። በዚሁ ድርጊት ቁጣቸውን እየገለጹ የሚገኙ የአካባቢው ነዋሪዎች አደጋው ወደ ደረሰበት ስፍራ ለመጓዝ ቢሞክሩም ...

Read More »

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር በተለያዩ ስፍራዎች ጥቃት ፈጸሙ

ኢሳት (መጋቢት 6 ፥ 2009) የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር ዞን የተለያዩ ስፍራዎች ማክሰኞ ምሽት ጥቃት ፈጸሙ። ከአይን ምስክሮችና ከንቅናቄው ምንጮች ለመረዳት እንደተቻለው በጭልጋ፣ ደንቢያና በጎንደር ዙሪያ ወረዳዎች በተመሳሳይ ቀንና በተቀራራቢ ሰዓት በመንግስት ሃይሎችና ተቋማት ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። በትግል ላይ እያሉ መስዋዕትነት በከፈሉት ሻለቃ መሳፍን ጥጋቡ ወይንም ገብርዬ እንዲሁም በታጋይ ጎቤ መልኬ እና በአበራ ጎባው ስም የተሰየሙት ወታደራዊ ዘመቻዎች፣ ...

Read More »

በአዲስ አበባ ቆሻሻ መድፊያ ቦታ በደረሰው አደጋ የሟቾች ቁጥር እያሻቀበ ነው።

መጋቢት ፭ (አምስት)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ በተለምዶ ቆሸ ሰፈር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በደረሰው አደጋ ሟቾች ቁጥር ከ90 በላይ የደረሰ ሲሆን፣ አሁንም በርካታ ዜጎች ከተቀበሩበት አፈር አልወጡም። ዛሬ ማክሰኞ ከ40ያላነሱ ሰዎች ተገኝተዋል። ከተገኙት አስከሬኖች መካከል ከወለደች 3 ወሩዋ የሆነችው አራስ እና የልጇ እንዲሁም ሁለት ቁራን በመቅራት ላይ የነበሩ ታዳጊዎች ይገኝበታል። ወላጆችም ዛሬም አካባቢውን ከበው ሲያለቅሱ ውለዋል። በጭንቀት ...

Read More »

ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የአውራሪስ ቀንድ ከኢትዮጵያ ወደ ታይላንድ ሊገባ ሲል ተያዘ

መጋቢት ፭ (አምስት)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ግምታቸው ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ 21 የአውራሪስ ቀንድ በሕገወጥ መንገድ ከኢትዮጵያ ወደ ታይላንድ ሊገባ ሲል በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን የታይላንድ ባለስልጣናት አስታወቁ። ባለፈው ዓርብ መነሻውን ከአዲስ አበባ አድርጎ ወደ ታይላንድ ከገባ አውሮፕላን ውስጥ ክብደታቸው 50 ኪሎ ግራም የሚመዝኑ በቦርሳዎች የተጫኑ ከተለመዱት የአውራሪስ ቀንዶች ለየት ያሉ እና ትላልቆች የአውራሪስ ቀንዶችን በታይላንድ አየር ማረፊያ ...

Read More »

በአዲስ አበባ ከቀናት በፊት ከደረሰው አደጋ የተረፉ ሰዎችን የማፈላለጉ ስራ ተጓትቷል ተባለ

ኢሳት (መጋቢት 5 ፥2009) በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀናት በፊት ከደረሰው አደጋ የተረፉ በርካታ ሰዎች የጠፉ ሰዎችን የማፈላለጉ ስራ ተጓትቷል በማለት ቅሬታ ማቅረብ ጀመሩ። ቅሬታ አቅራቢዎቹ አሁንም ድረስ ከፍራሹ ሊወጡ ያልቻሉ ሰዎች መኖራቸውንና ፍለጋው ከተጠበቀው በላይ መጓተት ማሳየቱን እንደገለጹ ቪኦኤ የእንግሊዝኛው ክፍል ቅሬታ አቅራቢዎችን ዋቢ በማድረግ ማክሰኞ ዘግቧል። “በአግባቡ የሚረዳን አካል ባለመኖሩ እራሳችን የቁፋሮ ስራ እያከናወንን ...

Read More »

በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ከሶስት ሺ በላይ መኖሪያ ቤቶች ለመልሶ ማልማት ፕሮጄክት ሊፈርሱ መሆኑ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 5 ፥2009) ክፍለ ከተማው የመኖሪያ ቤቶቹን ለማፍረስ በቅርቡ የተዋወቀው 10ኛው የከተማዋ የተሻሻለ የማስተር ፕላን በከተማው አስተዳደር መጽደቁን እየተጠበቀ የሚገኝ ሲሆን፣ እንዲፈርሱ የተወሰነባቸው 3ሺ 221 መኖሪያ ቤቶች ከ12 አመት በፊት የተገነቡ መሆናቸውን አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል። የተወሰኑ መኖሪያ ቤቶች ከ20 አመት በፊት የተገነቡ መሆናቸው ታውቋል። የየካ ክፍለ ከተማ እንዲፈርሱ በተወሰነባቸው አካባቢዎች የከተማ አስተዳደር የመልሶ ማልማት ፕሮጄክቶችን ለማካሄድ እቅድ እንዳለው ...

Read More »

በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተፈጠረው አደጋ የሟቾች ቁጥር 72 መድረሱ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 5 ፥2009) በአዲስ አበባ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተፈጠረው አደጋ የሟቾች ቁጥር እየጨመረ በመሄድ ማክሰኞ ምሽት ድረስ ቁጥሩ 72 መድረሱ ተገለጸ። በአካባቢው በሚደረገው ፍለጋ ለአራተኛ ቀን ቀጥሎ የሚገኝ ሲሆን፣ የሟቾች ቁጥር እያሻቀበ ሊሄድ እንደሚችል የተለያዩ አካላት በመግለጽ ላይ ናቸው። ከአደጋው የተረፉ ሰዎች በቆሻሻ ክምሩ አቅራቢያ ወደ 300 የሚደርሱ ሰዎች ይኖሩ እንደነበር ይገልጸዋል። ይሁንና የነዋሪዎቹ ትክክለኛ ቁጥሩ በአግባቡ ...

Read More »

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለተከሰተው የህይወት መጥፋት አደጋ የኢትዮጵያ መንግስት ተጠያቂ ነው አለ

ኢሳት (መጋቢት 5 ፥2009) በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከ60 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ሞት ምክንያት ለሆነው አደጋ የኢትዮጵያ መንግስት ተጠያቂ ነው ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ። የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ መንግስት በርካታ ሰዎች በቆሻሻ ክምር አጠገብ ለብዙ ጊዜያት ሲኖሩ ዝም ብሎ መመልከቱንና አደጋው ቀድሞ ሲወሰድ በሚችል የጥንቃቄ እርምጃ መከላከል ይቻል እንደነበር ገልጿል። የአካባቢው ነዋሪዎች ለባዮ-ፊዩል የሃይል ማመንጫ ፕሮጄክት ...

Read More »