.የኢሳት አማርኛ ዜና

በሰሜን ኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች የሚፈጸመው ጥቃት ቀጥሎአል

መጋቢት ፲፩ (አሥራ አንድ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አርበኞች ግንቦት7 ሰሞኑን በተከታታይ ካደረጋቸው ጥቃቶች መካከል አንዱ የሆነ ጥቃት በደንቢያ ከተማ ባለፈው ቅዳሜ ለሁለተኛ ጊዜ ተፈጽሟል። የከተማዋ ነዋሪዎች እንደተናገሩት ጥቃቱን ተከትሎ ከተማዋ እንደገና በወታደሮች የተወረረች ሲሆን፣ በርካታ ሰዎች ጥቃት ፈጻሚዎችን አጋልጡ እየተባሉ ክፉኛ ተደብድበዋል። በጯሂት ከተማ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎም እንዲሁ በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሟል። በደንቢያ ለሁለተኛ ጊዜ የተፈጸመው ጥቃት ...

Read More »

ብአዴን ሚስጢሮች የሚወጡት ለፓርቲው ህልውና የሚያስቡ ከፍተኛ አመራሮች በመጥፋታቸው ነው አለ

መጋቢት ፲፩ (አሥራ አንድ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ብአዴን ሚስጢሮቹ የሚባክኑት እንዲሁም በድርጅቱ ውስጥ ያለው አለመተማመን እንዲጨምር ያደረገው ከፍተኛ አመራሩ በድርጀቱ ላይ እምነት እያጣ በመምጣቱ ነው ሲሉ የብአዴንና የህወሃት ባለስልጣናት ተናግረዋል። ብአዴን ቅዳሜ ባካሄደው ስብሰባ ፣ ከብአዴን መሪዎች አቶ አለምነው መኮንን፣ ከህወሃት ደግሞ አቶ ኢሳያስ ወልደ ጊዮርጊስ በስልክ የተሳተፉ ሲሆን፣ ህወሃት የብአዴን ከፍተኛው አመራር እንዲሁም የክልሉ ሚዲያ እና ጋዜጠኞች ...

Read More »

የዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የቲማቲም ኩባንያ በአገሪቱ የሚታየውን የቲማቲም እጥረት ተከትሎ ከፍተኛ ሽያጭ እያካሄደ ነው

መጋቢት ፲፩ (አሥራ አንድ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና አሁን ለአለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርነት የሚወዳደሩት የህወሃቱ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ሸዋ እና በአርሲ ዞኖች ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን ገዝተው የቲማቲም እርሻ እያኬዱ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ እና በዋና ዋና የአገሪቱ ከተሞች የታየውን የቲማቲም እጥረት ተከትሎ፣ ከፍተኛ ገቢ እያገኙ ነው። በአዲስ አበባ ...

Read More »

በአዳማ ከተማ የውሃ እጥረት እና የመብራት መቆራረጥ ተባብሶ ቀጥሏል

መጋቢት ፲፩ (አሥራ አንድ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዳማ ከተማ እና አካባቢዋ የውሃ እጥረት እና የመብራት መቆራረጥ ችግር ተባብሶ በመቀጠሉ ነዋሪዎቹ ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን አስታወቁ። አገልግሎት ይሰጥ የነበረው የቀድሞው የውሃ ማጣሪያ ከከተማዋ ስፋት እና ሕዝብ ብዛት ጋር ተመጣጣኝ አለመሆኑን ተከትሎ የውሃ አቅርቦቱ ላይ መስተጓጎል ያስከተለ ከመሆኑን በተጨማሪ የከተማዋ አስተዳደር ንጹሕ ውሃ ለተጠቃሚዎች ለማዳረስ ምንም ዓይነት እርምጃዎችን ሲወስድ አልታየም። የኦሮሚያ ...

Read More »

በተለምዶ “ቆሼ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተቀበሩ ሰዎችን ለማግኘት ወራትን ሊፈጅ ይችላል ተባለ

ኢሳት (መጋቢት 11 ፥ 2009) በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ “ቆሼ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰው አደጋ በቆሻሻ ክምር የተቀበሩ ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ ለማግኘት ወራትን ሊፈጅ እንደሚችል የነብስ አድን ሰራተኞች አስታወቁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍለጋን የማካሄዱ ዘመቻው ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል ቢልም፣ የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ድረስ ከ80 የሚበልጡ ሰዎች አለመገኘታቸውን ገልጸዋል። የነብስ አድን ሰራተኞች በበኩላቸው በቆሻሻ ክምሩ ያልተገኙ ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ ፈልጎ ...

Read More »

የኢትዮጵያ መድሃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተርና ምክትላቸው ከሃገር ኮበለሉ

ኢሳት (መጋቢት 11 ፥ 2009) የበርካታ ሚሊዮን ብር ብክነት ሪፖርት የቀረበባቸው የኢትዮጵያ መድሃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተርና ምክትል ዋና ዳይሬክተር ከሃገር መኮብለላቸውን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። ሁለቱ ባለስልጣናት ከሃገር የኮበለሉት ስራቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁ በኋላ መሆኑንም መረዳት ተችሏል። ባሳለፍነው ታህሳስ ወር የ16 ሚሊዮን 863 ሺ 33 ብር ከደምብ ውጭ ህገወጥ የመድሃኒት ግዢ ፈጽመዋል በሚል በፓርላማ ሪፖርት የቀረበባቸው ዋናው ዳይሬክተር አቶ መስቀሌ ...

Read More »

ለስኳር ፕሮጄክቶች ግንባታና ማስፋፊያ ከህንድ የተወሰደው ከ700 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር የታሰበውን ውጤት አለማምጣቱ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 11 ፥ 2009) የኢትዮጵያ መንግስት በተለያዩ ጊዜያት ከህንድ ለስኳር ፕሮጄክቶች ግንባታና ማስፋፊያ የወሰደው ከ700 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር (ከ140 ቢሊዮን ብር በላይ) የታሰበውን ውጤት አለማምጣቱ ተገለጸ። ለእነዚሁ ፕሮጄክቶች በአምስት ዙሮች በድምሩ 739 ሚሊዮን ዶላር ብድር መለቀቁንና ባንካቸው ፋይናንስ ያደረጋቸው የስኳር ልማት ፕሮጄክቶች ውጤታማ መሆን እንዳልቻሉ የህንድ የኤክስፖርትና ኢምፖርት (ኤግዚም) ባንክ ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆኑት ዲባሲህ ማሊክ ለሪፖርተር ጋዜጣ ...

Read More »

አርበኞች ግንቦት7 ተከታታይ ጥቃቶችን መፈጸሙን ተከትሎ ሰሜን ጎንደር ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት አለ

መጋቢት ፰ (ስምንት)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአካባቢው ምንጮች እንደሚሉት ሰሞኑን በተለያዩ ታጋዮች ስም የተሰነዘሩት ጥቃቶችን ተከትሎ በአካባቢው ወታደራዊ እንቅስቃሴው ተጠናክሮ በመቀጠሉ ወታደሮች ታጋዮችን ጠቁሙ በማለት ህዝቡን እያስጨነቁት ነው። ቆላ ድባ በመስተዳድሩ ላይ የቦንብ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ሚሊሺያውና ወታደሮች እየተወዛገቡ ሲሆን፣ ዛሬም ከተማው ተወጥሮ ማወሉን የአካባቢው ምንጮቻችን ገለጸዋል። በጭልጋ ወረዳ አቦ ከተባለው ቦታ ላይ ትናንት ከምሽቱ 12:30 ላይ ታጋዮች ...

Read More »

የብአዴን ባለስልጣናት ኢሳት በሚያውጣቸው መረጃዎች ዙሪያ ክርክሮችን አካሄዱ

መጋቢት ፰ (ስምንት)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢሳት ብአዴንን አስመልክቶ የሚያወጣቸው መረጃዎች የብአዴንን ባለስልጣናት እርስ በርስ እያወዛገባቸው ነው።በአንዳንድ አመራሮች መካከል አለመተማመኑ እየሰፋ ሂዷል። የአማራ ክልል ጋዜጠኞች ከክልሉ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ጋር ያደረጉት ስብሰባ የድምጽ ቅጂ ፣ በፌደራል ደረጃ በሚጠበቅ ተቋምና ከፍተኛ የኤሌክቶሪንክስ ፍተሻ በተደረገበት ሁኔታ እንዴት በኢሳት ሊወጣ ቻለ የሚል ጥያቄ ተነስቶ ባለስልጣኖቹ የተወዛገቡ ሰሆን፣ የኮሚኒኬሽን ሃላፊው አቶ ንጉሱ ...

Read More »

በዝዋይ የሚታየው ከፍተኛ የውሃ እጥረት እንደቀጠለ ነው

መጋቢት ፰ (ስምንት)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የዝዋይ ሃይቅ ሼር በሚባለው የሆላንድ አበባ እርሻ በሚለቀው አደገኛ ኬሚካል የተነሳ፣ ህዝቡ ከሃይቁ ተጣርቶ የሚመጣውን ውሃ መጠቀም ካቆመ ሳምንታት ቢቆጠሩም፣ የኦሮምያ ክልል ባለስልጣናት መፍትሄ ሊሰጡት አልቻሉም። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ባለስልጣናት ህዝቡ ከሃይቁ የሚመጣውን የቧንቧ ውሃ እንዳይጠቀም ቢከለክሉም፣ አማራጭ መፍትሄ ግን አላስቀመጡም። የከተማው ህዝብ ከከተማው ውጭ በመኪና እየተጫነ የሚመጣለትን ውሃ እየገዛ ለመጠቀም ተገዷል። ...

Read More »