.የኢሳት አማርኛ ዜና

ከዋልድባ ገዳም ተቃውሞ ጋር በተገናኘ 39 የገዳሙ መነኩሴዎች መታሰራቸው ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 25 ፥ 2009) በቅርቡ ለእስር የተዳረጉት የዋልድባ ገዳም መነኩሴ አባ ገብረየሱስ ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት መወሰዳቸውንና የስቃይ ሰለባ ይሆናሉ የሚል ስጋት እንዳደረበት የዋልድባን እንታደግ ማህበር ሰኞ አስታወቀ። በአጠቃላይ 39 የዋልድባ ገዳም መነኩሴዎች መታሰራቸውንም መረዳት ተችሏል። አባ ገብረየሱስ የዋልድባ ገዳሙ ለልማት መነካት የለበትም በማለት ሲያሰሙ የቆዩትን ተቃትሞ ተከትሎ በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ክትትል ሲደረግባቸው ቆይቶ ከሁለት ወር በፊት ታፍነው መወሰዳቸውን ...

Read More »

በጎንደር ከተማ አንድ ሆቴል ውስጥ ጥቃት ተፈጽሞ በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

ኢሳት (መጋቢት 25 ፥ 2009) በጎንደር ከተማ ፍሎሪዳ ኢንተርናሽናል ሆቴል ላይ ቅዳሜ ምሽት የቦምብ ጥቃት ደረሰ። ጥቃቱ የተፈጸመበት ባለሶስት ኮከብ ሆቴል በአብዛኛው የወታደራዊ አዛዥ ጄኔራሎችና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የሚያርፉበት እንደኾነ እማኞች ለኢሳት ገልጸዋል። ማራኪ ተብሎ በሚታወቀው የጎንደር ዩኒቨርስቲ አካባቢ በሚገኘው በዚሁ ሆቴል የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ ሶስት ሰዎች መቁሰላቸውን ለማወቅ ተችሏል። ለጥቃቱ እስካሁን ሃላፊነት የወሰደ አካል የለም። በዚሁ በፍሎሪዳ ኢንተርናሽናል ሆቴል ...

Read More »

የህወኃትና ኢህአዴግ ከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ አባይ ጸሀዬ የመንግስትንና የፓርላማውን አሠራር አጠንክረው ነቀፉ።

መጋቢት ፳፭ (ሃያ አምስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- እምነት ያጣንበት ሚኒስትር ዳግም እየተሾመ ነው ያሉት አቶ አባይ፤ የመንግስት አሠራር ካልተቀየረ ይች ሀገር በእሳት ትቃጠላለች ሲሊ አስጠንቅቀዋል። ኢሳት በደረሰው የድምጽ መረጃ ላይ በፓርላማው የተለመደ የደቦና የጥድፊያ አሰራር ትችት የሰነዘሩት አቶ አባይ፤ ሹመትና በጀት ያለብስለትና ያለ እምነት በጥድፊያና በዘመቻ እየጸደቀ አፈጻጸም ላይ ከፍተኛ ችግር ማስከተሉን ጠቁመዋል። ቋሚ ኮሚቲው ከአስፈጻሚው የመጣውን ማጽደቅ ...

Read More »

ትናንት ምሽት በጎንደር ከተማ የቦንብ ጥቃት ተፈጸመ

መጋቢት ፳፭ (ሃያ አምስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢሳት ምንጮች ከስፍራው ባደረሱን መረጃ የትናንት ምሽቱ ከፍተኛ ፍንዳታ ከሰሞኑ በከተማዋ ለሦስተኛ ጊዜ የደረሰ ፍንዳታ ነው። በከተማዋ ማዕከል ላይ በሚገኘው በፍሎሪዳ ኢንተርናሽናል ሆቴል ትናንት ምሽት በተፈጸመው የቦምብ ፍንዳታ ሦስት ሰዎች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ኣስካሁን የሞተ ሰው ስለመኖሩ አልተነገረም። አካባቢውን ባናወጠው በዚህ ፍንዳታ የፍሎሪዳ ሆቴል መስኮቶች መሰባበራቸውንና በሌሎችም የሆቲሉ ንብረቶች ላይ ጉዳት ...

Read More »

የኢትዮጵያ መንግስት የአስቸኳይ የጊዜ አዋጁን ማራዘሙ ሕዝባዊ ቁጣውን አያቆመውም ሲል የምስራቅ አፍሪካ የሰብዓዊ መብት ሊግ አስታወቀ

መጋቢት ፳፭ (ሃያ አምስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለተጨማሪ አራት ወራት ማራዘሙን ለዓለምአቀፉ ማህበረስብ ማስታወቁ ሕዝባዊ እምቢተኝነቱን ሊያስቆመው አይችልም ሲል የምስራቅ አፍሪካ የሰብዓዊ መብት ሊግ መግለጫ አወጣ። ሚሊዮኖችን ከነባር ይዞታ ያፈነቀለውን የመሬት ቅርምት በመቃወም እና በአገሪቱ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በማውገዝ በሰላማዊ መንገድ ገዥው መንግስትን ሲቃወሙ የነበሩትን የአማራ እና ኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ...

Read More »

ኢትዮጵያ የአህያ ሥጋ ወደ ውጪ መላክ ጀመረች

መጋቢት ፳፭ (ሃያ አምስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአዲስ አበባ 48 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ቢሾፍቱ ወይም ደብረዘይት የተገነባው የአህያ ማረጃ መጠናቀቁንና ሥራ መጀመሩን ተከትሎ ኢትዮጵያ የአህያ ሥጋ ለውጪ ገበያ ማቅረብ መጀመሯን ሳምንታዊው አዲስ ፎርቹን ዘግቧል። እንደ መገናኛ ብዙሀን ሪፖርት ሻንዶንግ ዶንግ የተሰኘው የአህዮች ማረጃ ቄራ ግንባታ 80 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል። ኩባንያው የአህያውን ሥጋ የሚልከው ወደ ቬትናም ...

Read More »

ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ልታስገባ መሆኗል አሳወቀች።

መጋቢት ፳፭ (ሃያ አምስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መዲናይቱን አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ የአኢትዮጵያ ከተሞችና የገጠር አካባቢዎች በኤሌክትሪክ ብርሀን እጦት በተቸገሩበት በአሁኑ ወቅት ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ 400 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ልታስገባ መሆኗን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት አስታውቀዋል። ፕሬዚዳንት ጆን ማጉፉሊ እንዳሉት ሀገራቸው 57 ትሪሊዮን ኪዩቢክ ጫማ የተፈጥሮ ጋዝ በመጠባበቂያነት ቢኖራትም የኃይል ማመንጫ ግድቦቿ ያሉባቸው አካባቢዎች በድርቁ ምክንያት በመቀነሳቸው ከፍተኛ የኃይል እጥረት አጋጥሟቸዋል። ...

Read More »

የብሪታኒያ መንግስት ኢትዮጵያን ጨምሮ በሰብዓዊ መብት ረገጣ ለሚታወቁት ሃገራት ለስለላ የሚረዱ ቁሳቁሶችንና የጦር መሳሪያዎችን እንደሚያቀርብ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2009) የብሪታኒያ መንግስት ኢትዮጵያን ጨምሮ በሰብዓዊ መብት ረገጣ ለሚታወቁት ሃገራት ለስለላ የሚረዱ ቁሳቁሶችንና የጦር መሳሪያዎችን በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ አንድ አለም አቀፍ ተቋም አስታወቀ። ሃገሪቱ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለሳውዲ አረቢያ፣ ባህሬንና፣ የቤንዙዌላ መንግስታት የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ሲያቀርብ መቆየቱን በመገናኛና በማህበረሰብ መብት መከበር ዙሪያ የሚሰራው ግሎባል ቮይስ የተለያዩ አካላትን መረጃ ዋቢ በማድረግ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል። መቀመጫውን በኔዘርላንድ አምስተርዳም ከተማ ...

Read More »

በኩዌት አንዲት ኢትዮጵያዊት ከሰባተኛ ፎቅ ላይ ስትወድቅ የሚያሳይ ቪዲዮ የቀረጸች አሰሪን በቁጥጥር ስር በማዋል ፖሊስ ምርመራ ጀመረ

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2009) የኩዌት ፖሊስ አንዲት ኢትዮጵያዊት ከሰባተኛ ፎቅ ላይ ልትወድቅ ስትል የሚያሳይ ቪዲዮ የቀረጸች አሰሪን በቁጥጥር ስር በማዋል ድርጊቱን በመመርመር ላይ መሆኑን አርብ አስታወቁ። ኢትዮጵያዊቷ ከፎቁ በመስኮት ከመውደቋ በፊት “ያዙዝ” የሚል የዕርዳታ ጥሪን በተደጋጋሚ ብታሰማም አሰሪዋ ኢትዮጵያዊቷን ከመታደግ ይልቅ ሰብዓዊነት ባልተሞላበት መንገድ ፀያፍ ቃላቶችን ስትጠቀም የሚያሳይ ቪዲዮ በመሰራጨት ላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል። ይኸው በተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች በመሰራጨት ...

Read More »

የመኢአድ ፕሬዚደንት አቶ ማሙሸት አማረ ከነወንድማቸው ጋር በኮማንድ ፖስቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ታወቀ

ኢሳት (መጋቢት 22 ፥ 2009) የቀድሞ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚደንት አቶ ማሙሸት አማረ ከወንድማቸው ጋር በኮማንድ ፖስቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ታወቀ። የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት አቶ ማሙሸት ከወራት በፊት ከደረሰባቸው የጤና እክል ተከትሎ ጸበል በመከታተል ላይ እንደነበሩ ገልጸዋል። የአቶ ማሙሸት አማረ ወንድም የሆኑት አቶ ግዛቸው አማረ፣ ለወንድማቸው ስንቅ ለማቀበል በሄዱ ጊዜ በአንድ ላይ በኮማንድ ፖስት አባላት ታፍነው መወሰደዳቸውን ለመረዳት ...

Read More »