ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደ ሃገሪቱ ልማት ባንክ በብድር ስም እየተራቆተ መሆኑን ምንጮች ገለጹ። ለባንኩ ፕሬዚደንት በጉቦ መልክ እጅግ ዘመናዊ ቤት የተሰራላቸው ቢሆንም፣ እርሳቸው የሚኖሩበት ግን ባንኩ በዋስትና በወረሰው ቤት ውስጥ መሆኑንም መረዳት ተችሏል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የህወሃት ንብረት ለሆነው ኤፈርት ኩባንያዎች ብድር ምንጭነት በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት፣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ቅርበት ያላቸው ባለሃብቶችም ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
በኢትዮጵያ አህዮች እንዲታረዱ መደረጉ ተቃውሞ ሊቀሰቀስ ይችላል ተባለ
ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009) በኢትዮጵያ አህዮች እንዲታረዱና ስጋና ቆዳቸው ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መወሰኑ በኢትዮጵያውያን ዘንድ እያነጋገረ ሲሆን፣ በአፍሪካዊቷ ቡርኪናፋሶም ያስከተለው ቁጣ በኢትዮጵያ ሊደገም እንደሚችል የፖለቲካ ተመልካቾች ይገልጻሉ። በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ድርጊቱ ተቃውሞና ቁጣ ማስከተሉን ማስታወስ ተችሏል። መንግስት ከእንግዲህ ፈቃድ አልሰጥም ያለ ቢሆንም፣ ከዚህ በፊት የሰጠውን ግን አልሰረዘም። የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በበኩሉ ለውጭ ገበያ ይቀርባል ተብሎ የታሰበው የአህያ ስጋ ...
Read More »በሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከይዞታቸው ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ
ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009) በሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከተጨማሪ ወታደራዊ ይዞታዎች ለቀው መውታጣቸውን የሃገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ። ቁጥራቸው ያልተገለጸው ወታደሮቹ በማዕከላዊ ሶማሊያ ከሚገኘውና ኤልቡር ተብሎ ከሚጠራ አስተዳደር ለቆ መውጣቱን የአካባቢው የክልል ባለስልጣናት ለመገናኛ ብዙሃን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ወታደሮች ለረጅም ጊዜ ተቆጣጥረው ከቆዩት አስተዳደር በምን ምክንያት ለቀው እንደወጡ የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን፣ የሶማሊያው ታጣቂ ሃይል አልሸባብ ኤልቡርን እንደተቆጣጠረ ቪኦኤ የእንግሊዝኛው ክፍል ዘግቧል። ...
Read More »የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከግብፅ ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ ገለጹ
ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009) የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በሽብርተኛ ላይ እየተደረገ ያለውን ዘመቻ ለማጠናከር ከግብፅ ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ ሰኞ ይፋ አድርገዋል። ከቀድሞው የግብፅ ፕሬዚደንት ሆስኒ ሙባራክ ከስልጣን መወገድ በሁዋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በ White House የተጋበዙት ፕሬዚደንት አብደል ፈታህ አልሲሲ በበኩላቸው ፕሬዚደንት ትራምፕ በጸረ-ሽብርተኛ ላይ የያዙትን አቋም እንደሚያደንቁና ተባብረው እንደሚሰሩ ምክክር መካሄዱን ለመገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል። ሁለቱ መሪዎች ለሰዓታት በዝግ ባካሄዱት ...
Read More »በዋልድባ ገዳም አቅራቢያ በአማራና በትግራይ ሚሊሺያዎች መካከል የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከተሎ ከሁለቱም ወገን የሰው ህይወት ጠፋ
ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009) በዋልድባ ገዳም አቅራቢያ በአማራና በትግራይ ሚሊሺያዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ከሁለቱም ወገን ታጣቂዎች ተገደሉ። ማክሰኞ መጋቢት 26, 2009 አም ለተቀሰቀሰው ግጭት መነሻ የሆነው በዋልድባ ገዳም ለሚከበረው አመታዊ የመድሃኒያለም በዓል የሚጓዙ የአማራ ሚሊሺያዎች ትጥቅ እንዲፈቱ በመጠየቃቸው እንደሆነም መረዳት ተችሏል። በታሪካዊው ዋልድባ አበረንታት ገዳም መጋቢት 27 ለሚከበረው አመታዊ የመድሃኒያለም የንግስ በዓል በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ከዋዜማ ቀናት ጀምሮ ወደገዳሙ ...
Read More »በሰንሜን ጎንደር ዞን በደንቢያ ወረዳ የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ጥቃት በመፈጸም በህወሀት ጦር ላይ ከፍ ያለ ኪሳራ አደረሱ።
መጋቢት ፳፮ (ሃያ ስድስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ታጋዮቹ ለኢሳት በላኩት መግለጫ መጋቢት 25 ለ 26 ሌሊት ከ 7፡00 እስከ 9፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ በሰራቫ ጣና በለስ መስኖ ፕሮጀክት ቻይና ካምፕ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ መሽጎ በነበርው የህውሐት መከላከያሰራዊት ላይ ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት በወሰዱት እርምጃ ሁለት የገዥው ፓርቲ ወታደሮችን እና ሁለት የመከላከያ ሾፌሮችን ሲገድሉ በስድስት ወታደሮች ላይ ከባድ የመቁሰል ...
Read More »ኢህአዴግ “የመገናኛ ብዙሀንን አኮላሽቻቸዋለሁ” ሲል በግምገማው ማመኑ ተገለፀ፡፡
መጋቢት ፳፮ (ሃያ ስድስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የህወሀትና የኢህአዴግ ከፍተኛ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አባይ ጸሐየ ከመገናኛ ብዙሐን አመራር እና ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዩች ጋር በነበረው ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር “መገናኛ ብዙሐንፀረ ህዝብ እና የልማት እንቅፋት እንዲሆኑአኮላሽተናቸዋል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ይህ ችግር ከፓርቲዎች ጋር በሚደረግ ድርድርና ከግለሰቦች ጋር በመካከር አይሰተካከልም ያሉት የህወሃት አመራሩ አቶ አባይ ፤ “ብዙሐን መገናኛዎች እና ምክር ...
Read More »ሙሉ በሙሉ በወርቅ የተለበጠው ታሪካዊው የጋምቤላ የሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል ጽላት መዘረፉን ሳምንታዊው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገበ።
መጋቢት ፳፮ (ሃያ ስድስት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በጋምቤላ ከተማ ውስጥ የሚገኘው ታሪካዊውየሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ጽላት ማነታቸው በማይታወቁ ግለሰቦች መዘረፉን የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ምእመናን ገልጸዋል። የደብሩ ካህናት በበኩላቸው ከየካቲት 24 ቀን 2009 ዓ.ም ቀን ጀምሮ ታቦቱ ከመንበሩ አለመኖሩን አሳውቀዋል፡፡ በ1941 ዓ.ም. በቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ሀይለስላሴ እንደተሰራ የሚነገርለት ይህ ታሪካዊ ቤተክርስቲያን ታቦቱ በቅርስነት ተይዞ ጥበቃ ሊደረግለት ...
Read More »መንግስት ለአባይ ግድብ ግንባታ በአሜሪካ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ገንዘብ ለማሰባሰብ የነበረው እቅድ ችግር እንዳጋጠመው ተገለጸ
ኢሳት (መጋቢት 25 ፥ 2009) የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመገንባት ባለው የአባይ ግድብ ግንባታ በተለይ በአሜሪካ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ገንዘብ ለማሰባሰብ የነበረው እቅድ ችግር እንዳጋጠመው ገለጸ። 6.5 ሚሊዮን ዶላር ለአሜሪካ መንግስት ለመክፈልና የተመሰረተበትን ክስ ለማቋረጥ መወሰኑንም አስታውቋል። ባለፈው አመት ሰኔ ወር የአሜሪካው ሴኪውሪቴስ ኤንድ ኤክስቼንጅ (American Securities and Exchange Commission) ኮሚሽን የኢትዮጵያ መንግስት የአሜሪካን ህግ በጣሰ መልኩ የቦንድ ሽያጭ አካሄዷል ሲል ...
Read More »በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በሚገኙ 38 እስረኞች ላይ የተፈጸመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት አቤቱታ እንዲመረመር ተወሰነ
ኢሳት (መጋቢት 25 ፥ 2009) የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙ 38 ተከሳሾች በተደጋጋሚ ሲያቀርቡ የቆዩት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አቤቱታ ምርመራ እንዲካሄድ ወሰነ። የልብ ስፔሻሊስቱን ዶ/ር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ 38ቱ ተከሳሾች ባለፈው አመት በነሃሴ ወር በእስር ቤቱ ደርሶ ከነበረው የእሳት ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ክስ ስር የሚገኙ ሲሆን፣ አቤቱታ አቅራቢዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ከተፈጸመባቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መካከል የምርመራ ...
Read More »