ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009) በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ፒያሳ ሰራተኛ ሰፈር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የሚኖሩ 10ሺ ነዋሪዎች ለመልሶ ልማት ከመኖሪያ ቀያቸው ሊነሱ መሆኑ ተገለጸ። ከተቆረቆረ ረጅም ጊዜ እንደሆነ በሚነገርለት በዚሁ አካባቢ በርካታ በቅርስነት መፍረስ የሌለባቸው ህንጻዎች ያሉ ሲሆን፣ የከተማዋ ነዋሪዎችና የታሪክ ምሁራን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል። አካባቢውን በቀጣዮቹ ስድስት ወራቶች ሙሉ ለሙሉ ለማፍረስ ሃላፊነት የተሰጠው ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ከህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ 669 ሰዎች መሞታቸው መረጋገጡን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ገለጸ
ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009) በኦሮሚያክ አማራና የደቡብ ክልሎች ሲካሄድ ከቆየው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ 669 ሰዎች መሞታቸው መረጋገጡን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ማክሰኞ ገለጸ። በጉዳዩ ዙሪያ ያካሄደውን ምርመራ አስመልክቶ ሪፖርቱን ለፓርላማ ያቀረበው ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል በቢሾቱ ከተማ ከእሬቻ በዓል አከባባር ጋር በተገናኘ የደረሰውን የሞት አደጋ ጨምሮ በተለያዩ ዞኖች የተፈጸሙ ግድያዎችን አቅርቧል። በኦሮሚያ ክልል 15 ዞኖች እና 91 ከተሞች በአማራ ...
Read More »የኢትዮጵያ መንግስት የተመድና የአውሮፓ ህብረት በአገሪቱ የተፈጸሙ ግድያዎችን ለማጣራት ያቀረበውን ጥያቄ እንደማይቀበል አስታወቀ
ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009) የኢትዮጵያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የአውሮፓ ህብረት በመቶዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ምክንያት የሆነውን ግድያ ለማጣራት ያቀረቡትን ጥያቄ እንደማይቀበል በይፋ ምላሽ ሰጠ። ሁለቱ አለም አቀፍ ተቋማት ባለፈው አመት በኦሮሚያ ክልል ተቀስቅሶ ከነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች የሃይል ዕርምጃ በመውሰድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን ሲገልጹ ቆየተዋል። ይኸው የጸጥታ ሃይሎች ግድያና የሰብዓዊ መብት ጥሰት በገለልተኛ አካል ...
Read More »የአህያ ቄራ ለመዝጋት የተወሰደውን ዕርምጃ በመቃወም የቻይናውን ኩባንያ ጉዳዩን ወደ አለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንደሚወስደው አስታወቀ
ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009) የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር በከተማዋ የሚገኘውን የአህያ ቄራ ለመዝጋት የወሰደውን ዕርምጃ በመቃወም የቻይናውን ኩባንያ ጉዳዩን ወደ አለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንደሚወስደው ማክሰኞ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የፋብሪካው መዘጋትን በተመለከተ እስካሁን ድረስ የሰጠው ምላሽ ባይኖርም የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የአህያ ማረጃ ቄራው እንዲዘጋ መወሰኑ ተገልጿል። ይሁንና የከተማው የአስተዳደር ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም የቄራው ባለቤት የሆነው የቻይናው ሻንዶንግ ዶንግ ኩባንያ ...
Read More »በደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አንድ ኢትዮጵያዊን ያቃጠሉ ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ዘመቻ እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ
ኢሳት (ሚያዚያ 9 ፥ 2009) የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አንድ ኢትዮጵያዊ በገዛ ሱቁ ውስጥ በእሳት ተቃጥሎ ህይወቱ እንዲያልፍ አድርገዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ዘመቻ እያካሄደ መሆኑን ሰኞ አስታወቀ። አሰቃቂ የተባለው ይኸው የወንጀል ድርጊቱ በምስራቃዊ የኬፕ ግዛት ስር በምትገኘው የምስራቅ ለንደን ከተማ አቅራቢያ ቅዳሜ ምሽት ላይ መፈጸሙን የደቡብ አፍሪካ የማሰራጫ ኮርፖሬሽን (SABC) ዘግቧል። ፖሊስ ድርጊቱ በምን ምክንያት ሊፈጸም እንደቻለ መረጃ አለመገኘቱን ገልጾ፣ የአካባቢው ...
Read More »የታንዛኒያ ፖሊስ በህገወጥ ገብተዋል የተባሉ 66 ኢትዮጵያውያንን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ
ኢሳት (ሚያዚያ 9 ፥ 2009) የታንዛኒያ ፖሊስ ወደ ሃገሪቱ በህገ-ወጥ መንገድ ገብተዋል የተባሉ 66 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታወቀ። ስደተኛ ኢትዮጵያውያኑ በአንድ ተሽከርካሪ ሆነው በመጓጓዝ ላይ እንዳሉ ከነዋሪዎች በደረሰ ጥቆማ በጸጥታ አባላት ሊያዙ መቻላቸውን ዘ-ሲቲዝን የተሰኘ የታንዛኒያ ጋዜጣ ሰኞ ዘግቧል። የሃገሪቱ የኢሚግሬሽን መምሪያ በበኩሉ በተለያዩ ጊዜያው ወደ ታንዛኒያ በህገ-ወጥ የሚገቡ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን አስታውቀዋል። የምቤያ ...
Read More »በሶማሌ ክልል በኮሌራ ወረርሽኝ በየዕለቱ ከ500 የሚበልጡ ሰዎች ለህመም እየተዳረጉ እንደሆነ ተገለጸ
ኢሳት (ሚያዚያ 9 ፥ 2009) በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል ሰዎች ሞት ምክንያት በሆነው የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ በየዕለቱ ከ500 የሚበልጡ ሰዎች ለህመም በመዳረግ ላይ መሆናቸው ተገለጸ። የተባበሩት መንግስታት እና የእርዳታ ድርጅቶች በበሽታው ወረርሽኝ ሰዎች በመሞት ላይ መሆኑን ቢያረጋግጡም መንግስት የሟቾች ቁጥርን ከመግለጽ ተቆጥቧል። ይሁንና የበሽታ ወረርሽኙ በመባባስ ላይ መሆኑን ተከትሎ በወረርሽኙ በተጠቁ በርካታ ወረዳዎች በየዕለቱ ከ500 የሚበልጡ ሰዎች በበሽታው እየተያዙ መሆኑ ተመልክቷል። ...
Read More »የውጭ ምንዛሬ እጥረት በመባባሱ ፋብሪካዎች ስራቸውን እንዲያቆሙ እያደረጋቸው ነው
ሚያዝያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኦሮምያና አማራ ክልሎች የተነሳውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ በአገሪቱ የሚታየው የውጭ ምንዛሬ እጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ፋብሪካዎች ድርጅቶቻቸውን እስከመዝጋት እየደረሱ ነው። የአገሪቱን የፋይናስ ስርዓት በተገቢው መንገድ ይመራል ተብሎ የተቋቋመው ብሄራዊ ባንክ ለንግድ ባንክ ከግል ባንኮች በተለየ የሚሰጠው የዶላር አቅርቦች የግል ባንኮች ለደንበኞቻቸው በቂ የውጭ ምንዛሬ እንዳያቀርቡ በማድረጉ ባንኮቹ የህለውና አደጋ ተደቅኖባቸዋል። አቶ ...
Read More »የዓለም የምግብ ድርጅት እና የሳኡዲ አረቢያ መንግስት በኢትዮጵያ ለድርቅ ጉዳተኞች እርዳታ ለገሱ
ሚያዝያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሳኡዲ አረቢያ መንግስት እና የዓለም የምግብ ድርጅት (WFP) በጋራ ኢትዮጵያ ውስጥ አፋጣኝ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው የርሃብ ተጠቂዎች የሚውል ረድኤት እርዳታ ለግሰዋል። በደቡባዊ ምስራቅ ኢትዮጵያ ሶማሊያ ክልል በድርቅ ምክንያት ለከፍተኛ ርሃብ ተጋላጭ ለሆኑ የ127 ሽህ 666 ዜጎችን ሕይወት ለመታደግ የሚያስችል ለድንገተኛ አገልግሎት የሚውል እርዳታ ሰጥተዋል። የሳኡዲ አረቢያ መንግስት በንጉስ ሳልማን የእርዳታ ማእከል አማካኝነት ...
Read More »ታንዛኒያ ውስጥ 66 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ተያዙ
ሚያዝያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- እሁድ እለት ሕጋዊ የመግቢያ ሰነድ ሳይዙ ወደ ታንዛኒያ የገቡ 66 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን መያዙን የታንዛኒያ የድንበር ፖሊስ አስታውቋል። ኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች በተጨናነቀ ሁኔት ተጭነው ሲገቡ በአካባቢው ነዋሪዎች ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ የፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ዳሂር ኪዳቫሻሪ ተናግረዋል። ኮማንደር ዳሂር ”ኢትዮጵያዊያኑን ስደተኞች የጫነውን መኪና በፓትሮል ተከታትለን መንገድ በመዝጋት ኢሶንጄ ከተማ መቃረቢያ ላይ ይዘናቸዋል። ...
Read More »