.የኢሳት አማርኛ ዜና

የሶማሊያው ፕሬዚደንት ሞሃመድ አብዱላሂ ከኢትዮጵያ ጋር ተፈጥሯል በተባለው አለመተማመን ዙሪያ ለመምከር አዲስ አበባ ገቡ

ኢሳት (ሚያዚያ 25 ፥ 2009) የሶማሊያው አዲስ ፕሬዚደንት ሞሃመድ አብዱላሂ ከኢትዮጵያ ጋር ተፈጥሯል በተባለው አለመተማመን ዙሪያ ለመምከር ረቡዕ በአዲስ አበባ ጉብኝት ማድረግ መጀመራቸውን ራዲዮ ፍራንስ ኢንተርናሽናል የሃገሪቱ ባለስልጣናት ዋቢ በማድረግ ረቡዕ ዘገበ። ፕሬዚደንት አብዱላሂ ኢትዮጵያን ከመጎብኘታቸው በፊት በአምስት ሃገራት ጉዞ ያደረጉ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ የሚኖራቸው ቆይታ አስፈላጊም እጅግ አስቸጋሪም ነው ሲሉ የአፍሪካ ቀንድ የታሪክ ምሁር የሆኑት ጀራልድ ፕሩኒየር ለራዲዮ ጣቢያው ...

Read More »

የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የአለም ሃገራት ለመገናና ብዙሃን ነጻነት መከበር ቁርጠኝነታቸው እንዲያሳዩ ጥሪ አቀረቡ

ኢሳት (ሚያዚያ 25 ፥ 2009) የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የተለያዩ አለም አቀፍ አካላት የአለም ሃገራት ለመገናኛ ብዙሃን ነጻነት መከበር ቁርተኝነታቸውን በተግባር እንዲያሳዩ አሳሰቡ። በየአመቱ ሚያዚያ 25 ፥ የሚከበረውን የአለም የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት ቀንን አስመልክቶ መልዕክትን ያስተላለፉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬስ የአለም ሃገራት መረጃዎችና ዜጎች በመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ማዋከብና ማስፈራራት በአስቸኳይ ማቆም ...

Read More »

በባህርዳር የደረሰውን ፍንዳታ ተከትሎ የፌደራል ፖሊሶች ታሰሩ

ሚያዝያ ፳፬ ( ሃያ አራት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የደረሰበትን ህዝባዊ ማዕቀብ መቋቋም የተነሳነው በህወሃት/ብአዴን የሚተዳደረው ዳሸን ቢራ ስሙን ባላገሩ ቢራ በሚል ቀይሮ ባህርዳር ላይ ያዘጋጀው የሙዚቃ ዝግጅት፣ ፍንዳታ መካሄዱን ተከትሎ ፖሊሶች በድንጋጤ በመተኮሳቸው የ2 ሰዎች ካለፈ በሁዋላ፣ ከፍተኛ ብስጭትና ሽንፈት የደረሰበት ገዢው ፓርቲ፣ “ይህን ያክል ጥበቃ ተመድቦ ፣ ይህን ያክል ወታደር ጥበቃ እያደረገ እንዴት ቦንብ ሊገባ ...

Read More »

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አዳዲስ ታንኮች ወደ አገር ገቡ

ሚያዝያ ፳፬ ( ሃያ አራት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሚያዚያ 24 ቀን 2009 ዓም ጠዋት በርካታ ቁጥር ያላቸው አዳዲስ ታንኮችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ሾፌሮች ገልጸዋል። በጅቡቲ ወደብ 200 የሚሆኑ አዳዲስ ታንኮች የተራገፉ መሆኑን የሚገልጹት የአይን እማኞች፣ ከእነዚህ መካከል የተወሰኑትን ታንኮች የጫኑ ሎቤድ መኪኖች ወደ ደብረዘይት ተንቀሳቅሰዋል። ከ7 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን መራባቸው በተነገረ በሳምንት በእርዳታ ...

Read More »

የእንግሊዝ መንግስት ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ ሲሄዱ ለደህንነት ሲባል መጎብኘት የሌለባቸውን ቦታዎች ይፋ አደረገ

ሚያዝያ ፳፬ ( ሃያ አራት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የእንግሊዝ መንግስት የውጭ ጉዳይ እና የጋራ ብልጽግና ጽ/ቤት ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ በሚያደርጓቸውን ማንኛውንም ጉዞዎች ለደህነታቸው አስጊ እና አደጋ ሊደርስባቸው ይችላል ያላቸውን አካባቢዎች ለይቶ አሳውቋል። የቱሪስት መስህብ ከሆኑት ደብረዳሞ እና የሃ በስተቀር ከኢትዮ-ኤርትራ ድንበር 10 ኪሎ ሜትር አካባቢ በሚገኙት ከአክሱም እስከ አዲግራት ባሉ ዋና መንገዶች ዜጎቹ እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል። በሱዳን ...

Read More »

በከተሞች ዙሪያ የሚኖሩ አርሶ አደሮች ተተኪ ቦታ ባለማግኘታቸው እየተንገላቱ መሆኑን ተናገሩ፡፡

ሚያዝያ ፳፬ ( ሃያ አራት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመርአዊ ከተማ ዙሪያ የሚገኙ አርሶ አደሮች እንደገለጹት ፣ በተለያዩ ሰበቦች የእርሻ መሬታቸውን ከተነጠቁ በኋላ፣ ተተኪ የመኖሪያ ቦታ ባለማግኘታቸው ቤተሰቦቻቸው በቤት ኪራይ እየተሰቃዩ ነው። ወይዘሮ ፈንታነሽ አድማሴ በመርዓዊ ዙሪያ በሚገኝ የገጠር ቀበሌ ነዋሪ ናቸው፡፡ከከተማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሚኖሩበት አካባቢና የእርሻ ቦታቸው በመካለሉ አሮጌ ቤታቸውን አድሰው ቤተሰቦቻቸውን ይዘው ለመኖር ተከልክለዋል፡፡የከተማ ...

Read More »

የኢሳት 7ኛ አመት በሙኒክ ጀርመን በተሳካ ሁኔታ ተከበረ

ሚያዝያ ፳፬ ( ሃያ አራት ) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢሳት አለማቀፍ የድጋፍ ኮሚቴ የበላይ መሪነት እና በሙኒክ የኢሳት ቤተሰቦች የተዘጋጀው የኢሳት 7ኛ አመት የልደት በአል በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አዘጋጆች ገልጸዋል። በእለቱ የክብር እንግዳ ሆነው የቀረቡት ከአሜሪካ የቢቢኤን ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድና የኢሳት ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም ነበሩ። ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ ፣ ባለፉት 25 አመታት የህወሃትን የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ በኢትዮጵያ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አራት ም/ፕሬዚደንቶቹን ከሃላፊነት አነሳ

ኢሳት (ሚያዚያ 24 ፥ 2009) የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ካሉት አምስት ምክትል ፕሬዚደንቶች አራቱን ማክሰኞ ሚያዚያ 24 ፥ 2009 ጀምሮ ከሃላፊነት አነሳ። አቶ ታደሰ ሃቲያ የክሬዲት (ብድር) ማኔጅመንት ምክትል ፕሬዚደንት፣ አቶ ተካ ይብራህ፣ የኮርፖሬት አገልግሎት፣ አልማዝ ጥላሁን የፋይናንስና ባንኪንግ ማኔጅመንት እንዲሁም አቶ ደረጀ አውግቸው የድጋፍ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚደንቱ ከሃላፊነታቸው የተነሱ ባለስልጣናት መሆናቸውን አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል። ከስልጣናቸው በተነሱ ምክትል ፕሬዚደንቶች ምክትል ...

Read More »

የውጭ ምንዛሪ እጥረት በድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያደረሰ ነው ተባለ

ኢሳት (ሚያዚያ 24 ፥ 2009) በኢትዮጵያ የተከሰተው የውጭ ምንዛሪ እጥረት በትልልቅ ድርጅቶች ላይም ከፍተኛ ተፅዕኖ ማምጣቱ ተገለጸ። በዚህም የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖትና ሎጂስቲክስ ኢንተርፕራይዝ ባጋጠመው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳቢያ አጠቃላይ ገቢው ባለፉት ዘጠኝ ወራቶች በ1.5 ቢሊዮን ብር መቀነሱን አስታወቀ። ይኸውም መንግስታዊ ተቋም በዘጠኝ ወራቶች ውስጥ 14.3 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰባሰብ ቢያቅድም በውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት 11.8 ቢሊዮን ብር አካባቢ ብቻ ማግኘቱን ...

Read More »

የአቶ አሰፋ ጫቦ ቀብር የሰነ-ስርዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ታወቀ

ኢሳት (ሚያዚያ 24 ፥ 2009) የአቶ አሰፋ ጫቦ የቀብር ስነስርዓት የፊታችን አርብ በአዲስ አበባ ቅድስ ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ታወቀ። አስከሬኑ ማክሰኞ ከዳላስ አሜሪካ የተነሳ ሲሆን፣ ሃሙስ ከሰዓት አዲስ አበባ እንደሚደርስም ከወጣው መርሃ ግብር መረዳት ተችሏል። ሚያዚያ 5 ቀን 2009 አም በ73 አመታቸው በዩ ኤስ አሜሪካ ቴክሳስ ግዛት ዳለስ ከተማ ያረፉት አቶ አሰፋ ጫቦ፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 21 ፥ 2009 በዳለስ ቅዱስ ...

Read More »