.የኢሳት አማርኛ ዜና

በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለአለም ጤና ድርጅት ተመራጭ እንዳይሆኑ ተቃውሞ አቀረቡ

ኢሳት (ግንቦት 8 ፥ 2009) ነዋሪነታቸው በዚህ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ የሆነ ኢትዮጵያውያን በአለም ጤና ድርጅት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ፊት ለፊት በመሰባሰብ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የድርጅቱ ተመራጭ እንዳይሆኑ ተቃውሞ አቀረቡ። ማክሰኞ ረፋድ ላይ በድርጅቱ ጽ/ቤት የተሰባሰቡት ኢትዮጵያውያን ዶ/ር ቴዎድሮስ ከገዢው ከኢህአዴግ መንግስት ጋር በሰብዓዊ መብት ጥሰት ዙሪያ ያላቸው የቆየ ትስስር ድርጅቱን ለመምራት እንደማያበቃቸው ሲቃወሙ ታይተዋል። በትናንትናው ዕለት ታዋቂ የጤና ባለሙያዎች ዶ/ር ...

Read More »

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አገራት ከሚገኙ ደንበኞች ያልተከፈለው የአገልግሎት ክፍያ ለፋይናንስ እጥረት መዳረጉን ገለጸ

ኢሳት (ግንቦት 8 ፥ 2009) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት ከደንበኞቹ ያልተከፈለው የአገልግሎት ክፍያ ለፋይናንስ እጥረት እንደዳረገው ይፋ አደረገ። አየር መንገዱ ለተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት መንግስታትና ተቋማት አገልግሎት የሰጠባቸው ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለረጅም ጊዜ ሳይከፈለው መቅረቱን ሲገለጽ እንደነበር ይታወሳል። ይኸው ለረጅም ጊዜ ሳይከፈል የቆየው ክፍያ በድርጅቱ የእለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ተፅዕኖን ማሳደሩን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ...

Read More »

የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት አቶ ዮናታን ተስፋዬ በተመሰረተበት የሽብርተኛ ክስ የጥፋተኝነት ብይን ሰጠ

ኢሳት (ግንቦት 8 ፥ 2009) የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር ዮናታን ተስፋዬ ላይ በተመሰረተበት የሽብርተኛ ክስ የጥፋተኝነት ብይን ማክስኞ ሰጠ። በተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች በሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዙሪያ ጽሁፎችን ሲያቀርብ የነበረው ዮናታን በኦሮሚያ ክልል ከተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ ከአመት በፊት ለእስር መዳረጉ ይታወሳል። በግንቦት ወር 2008 አም ክሱን የመሰረተው ከሳሽ አቃቤ ህግ ተከሳሹ በማህበራዊ ድረገጾች አመፅ እንዲስፋፋ ...

Read More »

በመቀሌና በባህርዳር ከነማ የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል በተፈጠረው ግጭት የባህርዳር ከነማ ጥፋተኛ ሆኖ እንዲቀጣ ውሳኔ ተላለፈ

ኢሳት (ግንቦት 8 ፥ 2009) በመቀሌ ከነማና በባህርዳር አቻው የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል በተፈጠረው ውዝግብና ግጭት የባህርዳር ከነማ ጥፋተኛ ሆኖ እንዲቀጣ ውሳኔ መተላለፉን የኢሳት ምንጮች ገለጹ። በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኩል የተላለፈው ውሳኔ የፊታችን አርብ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።  ዕርምጃው ፖለቲካው ይዘት ያለው ነው የሚለውን ለመከላከል ከዳኞቹና ከውድድር ኮሚቴ በተገኘ መረጃ ላይ ተመርኩዞ ውሳኔው መተላለፉን የሚገልጽ ደብዳቤ መዘጋጀም ትመአልክቷል። የእግር ...

Read More »

ደህዴን በትግራይ ክልል በ12 ሚሊዮን ብር ያስገነባው ትምህርት ቤት መመረቁ ተገለጸ

ኢሳት (ግንቦት 8 ፥ 2009) የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደህዴን) በትግራይ ክልል በ 12 ሚሊዮን ብር ያስገነባው ህንጻ መመረቁ ተዘገበ።  መንግስታዊው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኤዜአ) እንደዘገበው በአቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የሚመራው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ በትግራይ ክልል አዲገባሮ በተባለ ገጠር ቀበሌ የሰራው 12 ሚሊዮን ብር የወጣበት ትምህርት ቤት ሰኞ ዕለት ተመርቋል። የደቡብ ክልል ለትግራይ ክልል ትምህርት ቤት ለመገንባት 12 ...

Read More »

መከላከያን ጥለው የሚጠፉ ወታደሮች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል

ግንቦት ፰ ( ስምንት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመከላከያ ምንጮች እንደገለጹት በቅርቡ በአማራና በኦሮምያ አካባቢዎች የተነሱትን ህዝባዊ ተቃውሞዎች ተከትሎ፣ ስርዓቱን በተለያየ መንገድ አናገለግልም በማለት እየጠፉ የሚሄዱ ወታደሮች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተከትሎ ገዢው ፓርቲ አዳዲስ ወታደሮችን በፍጥነት ለመመልመልና በተለያዩ መንገድ ከመከላከያ የተሰናበቱትን ተመልሰው እንዲገቡ ጥሪ ለማድረግ ተገዷል። ባለፉት 4 ወራት በርካታ ቁጥር ያላቸው ወታደሮች መጥፋታቸው ለመከላከያ ከፍተኛ ...

Read More »

በሃረሪ ክልል የሚገኙ የኦሮሞ የአገር ሽማግሌዎች መብታችን ካልተከበረልን ወደ ኦሮምያ እንጠቃለል አሉ

ግንቦት ፰ ( ስምንት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሃረሪ ክልል በገጠር አካባቢ የሚኖሩ የኦሮሞ አገር ሽማግሌዎች ለኦሮምያ ክልል ፕሬዚዳንት በጻፉት የአቤቱታ ድብዳቤ በሃረሪ ክልል ውስጥ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር ከፍተኛ ቢሆንም፣ ከፖለቲካና ከኢኮኖሚ ጉዳዮች ውጭ በመሆናችን አስቸኳይ የማስተካከያ እርምጃ የማይወሰድ ከሆነ ወደ ኦሮምያ ክልል እንድንጠቃለል እንጠይቃለን ብለዋል። ከ99 በመቶ በላይ የሚሆኑ በክልሉ የሚገኙ የንግድ ቤቶች እና ቦታዎች የተያዙት ...

Read More »

ወጣት ዮናታን ተስፋዬ በፌስቡክ ጽሁፎቹ በሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ ተባለ

ግንቦት ፰ ( ስምንት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሕግ አግባብ ውጪ ተይዞ ከዓመት በላይ በእስር ሲሰቃይ የቆየው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበረው ዮናታን ተስፋዬ በቀረበበት የሽብር ክስ ጥፋተኛ ተብሎአል። በፌስ ቡክ እና ትዊተር ጨምሮ በተለያዩ ማህበራዊ ድረገጾች ላይ በሚጽፋቸው ጽሁፎች ምክንያት ለእስር የተዳረገው ዮናታን ተስፋዬ የፀረ ሽብር አዋጁን 652/2001 አንቀፅ 6ን ተላልፈሃል በሚል የጥፋተኝነት ፍርድ ...

Read More »

በአማራ ክልል ዕምነት አልተጣለባቸውም የተባሉ የፖሊስ አመራሮች ከሃላፊነትና ከደረጃቸው ዝቅ ተደረጉ

ኢሳት (ግንቦት 7 ፥ 2009) በአማራ ክልል ከተካሄደው የጸጥታና ደህንነት ግምገማ ጋር በተያያዘ በህወሃት ዕምነት አልተጣለባቸውም የተባሉ የፖሊስ አመራሮች ከሃላፊነትና ከደረጃቸው ዝቅ ተደረጉ። ከክልሉ የፖሊስ አመራሮች ከስራ የተሰናበቱም ይገኙበታል። በባህርዳርና በጎንደር ከተፈጸሙት የቦምብ ጥቃቶች ጋር በተያያዘ የአካባቢው ጸጥታ አልተቆጣጠራችሁም የተባሉት የክልሉ ፖሊስ አባላት ስም ዝርዝር ኢሳት ደርሶታል። የአማራ ክልል አመራር አባላት ከስራ ደራጃቸው ዝቅ የተደረጉትና የተባረሩት የትምክህት አስተሳሰብ ሰለባ ናችሁ ...

Read More »

ዶ/ር ቴዎድሮስ የኮሌራ በሽታ እንዳይታወቅ ደብቀዋል ተብለው በአለም አቀፍ የጤና ባለሙያዎች ክስ ቀረበባቸው

ኢሳት (ግንቦት 7 ፥ 2009) ኢትዮጵያን በመወከል ለአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርነት ተፎካካሪ ሆነው የቀረቡት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበሩ ጊዜ በሃገራቸው የተከሰቱ ሶስት የኮሌራ ወረርሽኝ በሽታዎች ለህዝብ እንዳይታወቅ አድርገዋል የሚል ቅሬታ በአለም አቀፍ የጤና ባለሙያዎች ቀረበባቸው።  የጤና ድርጅቱ አባል ሃገራት የመጨረሻ እጩ ሆነው ከቀረቡ ሶስት ተፎካካሪዎች መካከል አንዱን ለመምረጥ የሳምንት ዕድሜ በቀራቸው ጊዜ ዶ/ር ቴዎድሮስ ላይ የቀረበው ...

Read More »