.የኢሳት አማርኛ ዜና

በቢሊዮን የሚቆጠር ብር የወጣባቸውና 25ሺ ያህል እስረኞችን የሚይዙ አዳዲስ ወህኒ ቤቶች በአራት ክልሎች ተገነቡ

ኢሳት (ሰኔ 20 ፥2009) በቢሊዮን ብሮች ወጪ 25 ሺህ ያህል እስረኞችን የሚይዙ ወህኒ ቤቶች በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ፣ በዝዋይና በሸዋሮቢት መገንባታቸው ታወቀ። አዲስ ፎርቹን የእንግሊዘኛ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ እንደዘገበው የአዲስ አበባ እስር ቤት 900 ሚሊዮን ብር የወጣበት ሲሆን በአንድ ጊዜ 6 ሺህ እስረኞችን የመያዝ አቅም አለው። በአዲስ አበባ ከተማ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አባሳሙኤል ወንዝ አቅራቢያ በ5ሺህ ስኩዌር ኪሎሜትር ላይ የተዘረጋው ...

Read More »

ቻይና በወንጀል የሚፈለጉ ቻይናውያን ለመቀበልና ወንጀል የፈጸሙ ኢትዮጵያውያንን አሳልፋ ለመስጠት ከኢትዮጵያ ጋር የተደረገውን ስምምነት አጸደቀች

ኢሳት (ሰኔ 20 ፥2009) ቻይና በወንጀል የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንንና ሌሎችን ለኢትዮጵያ አሳልፋ ለመስጠት እንዲሁም በወንጀል የምትፈልጋቸውን ቻይናውያንና ሌሎችን ከኢትዮጵያ ለመቀበል የተደረሰውን ስምምነት አጸደቀች።  የቻይና ዜና አገልግሎት ዥንዋ እንደዘገበው የቻይና ብሄራዊ ህዝባዊ ኮንግረስ ቋሚ ኮሚቴ ማክሰኞ ሰኔ 20/2009 ባካሄደው ስብሰባ ኢትዮጵያና አርጀንቲና በወንጀል የሚፈልጓቸውን ግለሰቦች አሳልፎ ለመስጠት የሚያስችለውን ስምምነት መሰረት ቻይና በወንጀል የምትፈልጋቸውን ግለሰቦች አርጀንቲናም ሆኑ ኢትዮጵያ ለቻይና አሳልፈው የመስጠት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። ...

Read More »

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ እና አቶ ሸፈራው ሽጉጤ በዘረጉት የሙስና ሰንሰለት ከፍተኛ ገንዘብ እየመዘበሩ መሆኑን መረጃዎች አመለከቱ

ሰኔ ፳ ( ሃያ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የቀድሞው የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት፣ የትምህርት ሚኒስትሩ ሸፈራው ሽጉጤ በዘረጉት ከፍተኛ የዝርፊያ ሰንሰለት በብዙ መቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ መዝረፋቸውን ከአስተማማኝ ምንጮች የተገኘው መረጃ አመልክቷል። የምንጮቻችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል፣ ምረመራውን ያካሄደውን የኦዲት ክፍል ለመግለጽ ባንችልም፣ መርምራውን የካሂዶት ኦዲተሮች ግማሾቹ ማስፈራሪያ ደርሶአቸው ስራቸውን ለቀዋል። አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከደቡብ ክልሉ ወንዶ ኢንዶውመንት ኩባንያዎች ...

Read More »

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኮማንደሮችን ስራ መልቀቅ በተመለከተ ለኢሳት ዘገባ መልስ ሰጠ

ሰኔ ፳ ( ሃያ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽኑ መልሱን የሰጠው ኢሳት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኪሚሽነር ኮማንደር አሰፋ ስንታየሁና የምዕራብ ጎጃም ዞን የወንጀል ምርመራ ሃላፊ የነበሩት ኮማንደር በላይ ካሴ ሃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው መልቀቃቸውን በማስመልከት ዘገባ ማቅረቡን ተከትሎ ነው። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሽብር ማህበራዊ ሚዲያ አራማጆች የአማራ ክልል ኪሚሽን ስራ ባልደረባ የሆኑት ኮማንደር አሰፋ ስንታየሁና ኮማንደር በላይ ...

Read More »

በማእከላዊ ዜጎች ከፍተኛ ድብደባ እየተፈጸመባቸው ነው

ሰኔ ፳ ( ሃያ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምንጮች እንደገለጹት ሸራተን እየተባለ በሚጠራው የእስር ቤቱ ክፍል የሚገኝ ዘርኣይ አዝመራው የሚባል ከደባርቅ አካባቢ የመጣ ወጣት አባትህ ሸፍቷል በሚል በአሌክትሪክ “ ሾክ” ስለተደረገ ሰውነቱ እንደሚንቀጠቅ፣ በራሱ መሄድ ባለመቻሉም በድጋፍ እንደሚጓዝ ታውቋል። ሌሎችም በሰሜን ጎንደር የተለያዩ ወረዳዎች ተይዘው የመጡ ዜጎች ከፍተኛ የሆነ ድብደባ የተፈጸመባቸው በመሆኑ ለአካል ጉዳት ተደርገዋል። አእምሮን በሚጎዳ ...

Read More »

አንድ ሺህ 438ኛው የኢድ አልፈጥር በአል በመላው አለም ተከበረ

ኢሳት (ሰኔ 19 ፥ 2009) በአዲ አበባ ታላቁ አንዋር መስጊድና በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተከበረው የኢድ አልፈጥር በአል ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ቁጥር በተገኙበት ዩ ኤስ አሜሪካ በተለይም በዋሽንግተን ዲሲ በደማቅ ስነ-ስርዓት መከበሩን ዜናው ያስረዳል። የፈርስት ሂጂራ ፋውንዴሽን ኢማም ሼህ ካሊድ ኡመር እና የፋውንዴሽኑ ፕሬዝዳንት ሃጂነጂብ መሃመድ በተገኙበት በዋሽንግተን ዲሲ አቅራቢያ ቨርጂኒያ ግዛት በተከበረው የኢድ አልፈጥር በአል ሙስሊሙ ማህበረሰብ በብዛት መገኘቱም ታውቋል። በከፍተኛ ...

Read More »

የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አጽም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል አረፈ

ኢሳት (ሰኔ 19 ፥ 2009) በርካታ ወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም አድናቂዎቻቸው በተገኙበት እሁድ ረፋድ ላይ በተካሄደው ስነ- ስርአት የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ ድርጅት አመራሮች ታዋቂ ሰዎች መታደማቸውም ተመልክቷል። የታዋቂው የህክምና ባለሙያ የመኢህድ መስራችና ፕሬዝዳንት የነበሩት የፕሮ/ር አስራት ወልደየስ መካነ- መቃብርና ሃውልት ላለፉት 18 አመታት ከነበረበት ባለወልድ ቤተክርስቲያን ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ እንዲነሳ መወሰኑ ቁጣ መቀስቀሱ ይታወቃል። እሁድ ሰኔ 18/2009 ፍልሰተ አጽማቸው በመንበረ ጸባኦት ...

Read More »

የመውጫ ቀነገደቡ ቢያበቃም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን አሁንም ከሳውዲ አለመውጣታቸው ተገለጸ

ኢሳት (ሰኔ 19 ፥ 2009) የሳውዲ አረቢያ መንግስት ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውን የውጪ ሐገር ዜጎች ሀገር ለቀው አንዲወጡ ያስቀመጠው ቀነ ገደብ ቢጠናቀቅም ከመቶ ሺዎች በላይ ኢትዮጵያዊያን ከሳውዲ አንዳልወጡ ህወሐት መራሹ መንግስት አመነ ። የጉዞ ሰነድ ከወሰዱት ወደ አገር ቤት የተመለሱት ከ 42 በመቶ በታች ነው።  የሳውዲ ኣረቢያ መንግስት ከመጋቢት 21 ቀን 2009 አ/ም ጀምሮ በነበሩበት ተከታታይ ሶስት ወራት ሕጋዊ የመኖሪያ ...

Read More »

የታዋቂው ገጣሚ ሻለቃ ክፍሌ አቦቸር አራተኛው የስነ-ግጥም መጽሃፉ ተመረቀ

ኢሳት (ሰኔ 19 ፥ 2009) “ሚስጥሯን-ያልገለጠልን” በሚል ርእስ በ175 ገጽ እና 61 የግጥም መድብሎችን የያዘው የስነ-ግጥም መጽሃፍ ቅዳሜ ሰኔ 24 ቀን 2017 በቨርጂኒያ አርሊንግተን የተመረቀ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የደራሲው ወዳጆችና አድናቂዎች እንዲሁም በኪነ-ጥበብ ዘርፍ ታዋቂ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል።  በምረቃው ዝግጅት ላይ “ትላንትን ማስታወስ፣ ነገን ማሰብ ካልተቻለ የዛሬ ፈተና አይተላለፍም” በማለት የእንኳን ደህና መጣችሁ የመግቢያ ንግግር ያደረገው የመጽሃፉ ደራሲ ሻለቃ ክፍሌ አቦቸር ...

Read More »

በሶማሌ ክልል ህጻናት በረሃብ እየሞቱ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን ይፋ አደረገ

ኢሳት (ሰኔ 19 ፥ 2009) በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ዶሎ ዞን በያዝነው ሰኔ ወር ብቻ 67 ሕጻናት በረሃብ መሞታቸውን ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን ሰኞ ይፋ አደረገ። 51 ህጻናት የሞቱት ወሩ በገባ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ እንደሆነም ተመልክቷል።  በኢትዮጵያ ሶማሌ ዞን ያለው የረሃብ ሁኔታ አስደንጋጭ ሆኖ መቀጠሉን ያስታወቀው የፈረንሳይው ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን 27 የመመገቢያ እንዲሁም አራት የህክምና እና የመመገቢያ ጣቢያ በማቋቋም ...

Read More »