(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 11/2009) የኤፈርት ንብረት የሆነውና በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማራው ትራንስ ኢትዮጵያ በ372 ሚሊየን ብር ያስገነባው ዋና መስሪያ ቤትና የጎማ አገልግሎት መስጫ ማእክል ተጠናቆ ስራ ጀምሯል። በ3 ሚሊየን ብር ካፒታል ክ650 የጭነት መኪናዎች በላይ በመያዝ የትራንስፖርት ዘርፉን በበላይነት የሚመራውና የህወሃት ንብረት እንደሆነ የሚታወቀው ትራንስ ኢትዮጵያ በ372 ሚሊየን ብር በአዲስ አበባ ያሰራውን ህንጻ አስመርቋል። ህንጻውን መርቀው የከፈቱት የኤፈርት ዋና ስራ አስፈጻሚ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
የኢንተር ኮንቲነንታል ባለቤት ከእስር ተፈቱ
(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 11/2009)የኢትዮጵያ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን በኢንተር ኮንቲነንታል ሆቴል ባለቤት አቶ ስማቸው ከበደ ላይ ክስ የመሰረተው እንደ ኣአውሮፓዊያን ኣአቆጣጠር በግንቦት 2013 ነበር። በዋናነት ክሱን ሲመሰርትም አቶ ስማቸው ከታክስ ማጭበርበርና ከሙስና ጋር በተያያዘ የሰሩት ወንጀል አለ በሚል ነው። ግለሰቡ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ከፍተኛ አመራር ከነበሩት ከአቶ መላኩ ፈንታና ከአቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ ጋር በመተባበር የሰሩት ወንጀል ግንኙነት አለው ...
Read More »የኢትዮጵያ ብረታብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ብሄራዊ ሃፍረትና ውርደት እየሆነ መምጣቱ ተገለጸ።
(ኢሳት ዜና–ሐምሌ 11/2009) መለዮ ለባሾቹ የሜቴክ አመራሮች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከስርአቱ ደጋፊዎችና አገልጋዮች እንዲሁም ከፓርላማ አባላት ሳይቀር መብጠልጠል ጀምረዋል። ይህ ደግሞ ሜይቴክን በተመለከተ በአገዛዙ ውስጥ ሁለት ጎራ እንዳለ አመላካች እንደሆነ ታዛቢዎች ይናገራሉ። በህወሃቱ ጄኔራል ክንፈ ዳኘው የሚመራው ሜይቴክ ለሃገር እየተሰዋን ነው ማለቱን የሚደገፍ በአንድ ጎራ፤ የሃገር ሃብት እየባከነና እየተዘረፈ ነው የሚሉት ደግሞ በሌላ ጎራ ተከፋፍለዋል። ለስርአቱ ቅርበት እንዳለው የሚነገረው የፎርቹን ...
Read More »ከግብር ጋር በተያያዘ የተጀመረው አድማ ለሁለተኛ ቀን ቀጥሎአል ሐምሌ ፲፩ ( አሥራ አንድ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በተለያዩ ከተሞች ከእለታዊ ገቢ ግብር ጋር በተያያዘ የተጀመረው የነጋዴዎች አድማ ለሁለተኛ ቀን ተጠናክሮ ቀጥሎአል። በአምቦ የንግድ ድርጅቶችና ሌሎች አገልግልሎት ሰጪ ተቋማት እንደተዘጉ ናቸው። በአምቦ መስመር ወደ አዲስ አበባ እና ወደ ወለጋ የሚሄዱ መንገዶች በመዘጋታቸው የተሸከርካሪ አግልግሎት ተቋርጧል። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌደራል ፖሊስ አባላት ከተማዋን ወረው እያንዳንዱን እንቅስቃሴ በመቆጣጠር ላይ ናቸው። በጊንጪም እንዲሁ የተቃውሞውን ጥሪ ባለማክበር ሲሰራ የተገኘ አንድ ሚኒባስ ተሽከርካሬ በድንጋይ ተሰባብሯል። በወሊሶም እንዲሁ አድማው ተጠናክሮ ቀጥሎአል። ሆቴሎችና ሱቆች ተዘጋግተዋል። የባጃጅ አገልግሎት ተቋርጧል። ፖሊሶች ከተማዋን ተቆጣጥረው ቅኝት እያደረጉ ነው። የክልሉ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ በአምቦ የተጀመረው አድማ በሰላም መጠናቀቁን ቢናገሩም፣ አድማው ግን ዛሬም ድረስ ለሁለተኛ ጊዜ እንደቀጠለ ነው። አድማው በበርካታ አነስተኛ ከተሞችም በመካሄድ ላይ ነው። በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች አድማውን እንዲቀላቀሉ ጥሪ የሚያደርጉ ወረቀቶች እየተበተኑ ነው። በደቡብ ኦሞ ዞን ዋና ከተማ ፣ ጂንካና በአካባቢው የሚገኙ ጋዘር፣ ቶልታ እና የመሳሰሉት ከተሞችም መንግስት የህዝቡን ገቢ፣ የኑሮ ሁኔታ ፣ እንዲሁም በየጊዜው ከህዝቡ በልማት ሥም በፈቃድና ጫና /ተጽዕኖ የሚሰበሰበውን ገቢና በባለሥልጣናት የሚመዘበረውን የህዝብ ሃብት ባላገናዘበ መንገድ የከመሩትን የቀን ገቢ ግምት ህዝቡ የማይቀበለው መሆኑ በግልጽ እየተነገረ ነው ፡፡ የንግዱ ማኅበረሰብ ዞናችን በድርቅ በተመታበትና የአርብቶአደር ህዝባችን የኑሮ መሰረት በተናጋበት ወቅት ‹አደጋውን በጋራ ለመመመከት በጋራ ምን ማድረግ እንችላለን› በሚል ሳያነጋግር፣ ዛሬ ‹‹ግብር ለመሰብሰብ መምጣቱን እንቃወማለን› እያሉ ነው።
ሐምሌ ፲፩ ( አሥራ አንድ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በተለያዩ ከተሞች ከእለታዊ ገቢ ግብር ጋር በተያያዘ የተጀመረው የነጋዴዎች አድማ ለሁለተኛ ቀን ተጠናክሮ ቀጥሎአል። በአምቦ የንግድ ድርጅቶችና ሌሎች አገልግልሎት ሰጪ ተቋማት እንደተዘጉ ናቸው። በአምቦ መስመር ወደ አዲስ አበባ እና ወደ ወለጋ የሚሄዱ መንገዶች በመዘጋታቸው የተሸከርካሪ አግልግሎት ተቋርጧል። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌደራል ፖሊስ አባላት ከተማዋን ወረው እያንዳንዱን እንቅስቃሴ በመቆጣጠር ...
Read More »አማራና ትግሬን እናስታርቃለን በሚል ህወሃት ያዘጋጀው ስብሰባ በራሱ ሽማገሌዎች ተተቸ
ሐምሌ ፲፩ ( አሥራ አንድ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመቀሌ ከተማ ለ3 ቀናት የአማራውና ትግራይን ህዝብ ለማስታረቅ የሚል አጀንዳ የተሰጠው ስብሰባ እክል ገጥሞታል። በብአዴንና በህወሃት የተመለመሉት የአገር ሽማግሌዎች፣ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እንደማያውቁ እየተናገሩ ነው። “በመጀመሪያ ህዝብ ከህዝብ አልተጣላም” የሚሉት ሽማግሌዎች፣ ያልተጣላን ህዝብ እንዴት አድርገው እንደሚያስታርቁ ግራ መጋባታቸውን ይናገራሉ። “ቁርሾው ያለው በህዝቡና በህወሃት መሪዎች መካከል እንጅ በትግራይና በአማራ ...
Read More »በእነ ንግስት ይርጋ ላይ ለመመስከር የተጠሩ ምስክሮች ሳይቀርቡ ቀሩ
ሐምሌ ፲፩ ( አሥራ አንድ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ በሴትነቷ ጥቃት እንደተፈጸመባት በቅርቡ ለህዝብ ይፋ ያደረገችው በሰሜን ጎንደር ተካሂዶ የነበረውን ህዝባዊ አመጽ በማስተባበር በተከሰሰችው ንግስት ይርጋ እና ሌሎች ተከሳሾች ላይ ሊቀርቡ የነበሩት የአቃቢ ህግ ምስክሮች ሳይቀርቡ ቀርተዋል። ፌደራል ፖሊስ የምስክሮችን አድራሻ አለማግኘቱን በመናገር ሌላ ቀጠሮ ጠይቋል። የተከሳሾች ጠበቃ አቃቢ ህግ ለ5ኛ ጊዜ ቀጠሮ ...
Read More »የያንግ ሩት እንግሊሽ እስኩል ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ጠፋ
ሐምሌ ፲፩ ( አሥራ አንድ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመዲናችን አዲስ አበባ የሚገኘው የያንግ ሩት እንግሊሽ እስኩል ትምህርት ቤት ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ጠፍትዋል። ተማሪዎቹ እና ወላጆች በውጤቱ መጥፋት ምክንያት ከፍተኛ ጭንቀት ላይ መውደቃቸውን የትምህርት ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ታፈሰ ዋቺሶ ለሸገር ኤፍኤም ሬዲዮ ተናግረዋል። የትምህርት ቤቱ አስተዳደር የፈተናውን ውጤት ለማግኘት የአዲስ አበባ ትምህርት ...
Read More »ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር ለመተባበርና ለመደራደር ምንጊዜም ዝግጁ መሆኗን ገለጸች
(ኢሳት ዜና–ሐምሌ 10/2009) ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ ጉዳይ ላይ ከግብጽ ጋር ለመተባበርና ለመደራደር ምንጊዜም ዝግጁ መሆኗን ገለጸች ። የግብጽ መንግስት ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ ውሀ ለመሙላት መዘጋጀቷን ተከትሎ ጉዳዩ እያሰሰበው መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል ። ይህንን ተከትሎም በኢትዮጵያ የግብጽ አምባሳደር የተመራ ቡድን አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳን በጉዳይ ላይ ማነጋገሩ ታውቋል። የግብጽ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት የኢትዮጵያ መንግስት በኣባይ ግድብ ጉዳይ ላይም ሆነ በሁለቱ ...
Read More »በኦሮሚያ ሕዝባዊ አምጹ በተለያዩ አካባቢዎች ተጠናክሮ ቀጥሏል
(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 10/2009) ከግብር ጫናና ትመና ጋር ተያይዞ እንደገና ያገረሸው ተቃውሞ በርካታ የኦሮሚያ አካባቢዎችን እያዳረሰ ይገኛል። በሕወሃት የሚመራው አገዛዝ በተለያዩ ተሽከርካሪዎች ወደ ኦሮሚያ ተጨማሪ ወታደሮችን እየላከ መሆኑ ተነግሯል። በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው አምጽ በአምቦ ጀምሮ ጊንጪና ጀልዱ እንዲሁም ወሊሶና ቡራዩን አዳርሷል። በሻሸምኔ፣በኮፈሌና አርሲም ተመሳሳይ ሕዝባዊ ተቃዋሚዎች መኖራቸው ነው የተነገረው። በጊንጪ የስራ ማቆም አድማ ሙሉ በሙሉ እየተደረገ መሆኑ ታውቋል።የንግድ ቤቶች፣ሱቆችና ሆቴሎች ተዘግተዋል። ...
Read More »ጋዜጠኛና ደራሲ ነጋሽ ገብረማርያም አረፉ።
(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 10/2009) አንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ ነጋሽ ገብረማርያም በ93 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። ስርአተ ቀብራቸው ሐምሌ 11/2009 በጉርድ ሾላ ሳህሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን እንደሚፈጸም ተነግሯል። አንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ ነጋሽ ገብረማርያም የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥንን በመምራትና የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆነው አገልግለዋል። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትና በሬዲዮ እንዲሁም በቴሌቪዥን በጋዜጠኝነት ሙያ ሲሰሩ በሙያው ዘመናዊ ትምህርት ከተማሩ የቀድሞ ጋዜጠኞች አንጋፋ እንደነበሩ የህይወት ...
Read More »